ሀዋሳ፡ የካቲት 10/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የተሻለ ተቋማዊ አደረጃጀትን መፍጠር ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ የላቀ በመሆኑ በተቀናጀ ርብርብ ሊሠራ እንደሚገባ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች ገለጹ፡፡
በክልሉ ታርጫ ማዕከል የሚገኙ የፓርቲ ቤተሰብ አባላት “ከቃል እስከ ባህል” በሚል መሪ ሃሳብ መነሻ በፓርቲው ሁለተኛ መደበኛ ጉባዔ ውሳኔና በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ተግባራቸውን ለማከናወን ተቀናጅተው እንደሚሠሩም አስረድተዋል።
በውይይታቸውም ከቀረበው ሰነድ መነሻ ለተግባር ውጤታማነት ትኩረት ተሰጥቶ ካልተሠራ የኑሮ ውድነትን መቅረፍ እንደማይቻልም ተገልጿል።
ተቋማዊ አቅም ግንባታ በተደራጀ ሁኔታ በማጠናከር ለጠንካራ ሀገር ግንባታ የድርሻቸውን ለመወጣት በተቀናጀ ርብርብ ተግባራቸውን እንደሚያከናውኑ ተናግረዋል።
አካታች የሆነው ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር ተቋማዊ አንድነትን ከመፍጠር ባለፈ
በክልሉ የተጀመሩ ኢንሼቲቮች ውጤታማ እንዲሆኑ በትኩረት መሥራት ተገቢ እንደሆነም ገልጸዋል።
አሁን ላይ በክልሉ የሚገኙ አመራሮች የፖለቲካ ተግባቦት ሥራ በተጠናከረ አኳኋን እያከናወኑ እንደሚገኙም ተገልጿል።
በማዕድን፣ በቡና፣ በቱሪዝምና በሌሎች የገቢ ማስገኛ ምንጮች ላይ በትኩረት በመሥራት ዜጎችን በየደረጃው ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችል ውጤት እንዲመዘገብ የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡም ነው የገለጹት።
ዘጋቢ፡ መሣይ መሠለ – ከዋካ ጣቢያችን
More Stories
በወላይታ ዞን ባለፉት 10 ወራት ውስጥ ህገ-ወጥ ንግድና ለመከላከል በተደረገው ክትትል 2 ሺህ 135 ነጋዴዎች ላይ የእርምት እርምጃ መውሰድ መቻሉን የዞኑ ንግድና ገበያ ልማት መመሪያ አስታወቀ
በ2017/18 የመኸር አዝመራ ከ4 መቶ ሺ ሄክታር በላይ ማሳን በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች መሸፈኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት የ10 ወራት አፈጻጸም እና የቀጣይ የክረምት ወራት ቅድመ ዝግጅት ግምገማ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ እያካሄደ ይገኛል