በዚህ መሰረትም ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ መቻል ከወልቂጤ ከተማ ጨዋታቸውን የሚያደርጉ ሲሆን÷ ሀዲያ ሆሳዕና
ከአዳማ ከተማ ምሽት 1 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ፡፡
ፕሪሚየር ሊጉን ቅዱስ ጊዮርጊስ በ22 ነጥብ ሲመራ ኢትዮጵያ መድን በግብ ክፍያ ተበልጦ በተመሳሳይ 22 ነጥብ ሁለተኛ በመሆን ይከተላል፡፡
የቅዱስ ጊዮርጊሱ ኢስማኤል ኦሮ- አጉሮ በ11 ጎል በከፍተኛ ጎል አግቢነት ሲመራ÷ የወልቂጤ ከተማው ጌታነህ ከበደ
በ10 ጎል ይከተላል፡፡
የፋሲል ከነማው ፍቃዱ አለሙ እና የድሬዳዋ ከተማ ቢኒያም ጌታቸው 7 ጎሎችን በማስቆጠር 3ኛ እና 4ኛ ደረጃን ይዘዋል፡፡
መርሐ ግብሩ ቀጥሎ÷ ማክሰኞ ቀን 10 ሰዓት ድሬዳዋ ከተማ ከወላይታ ዲቻ፣ ምሽት 1 ሰዓት ሲዳማ ቡና ከ ባህርዳር ከተማ ጫዋታቸውን እንደሚያደርጉ ከሊግ ኩባንያው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

More Stories
አርሰናል በአስቶንቫላ ተሸነፈ
ኮቢ ሜይኑ ማንቸስተር ዩናይትድን መልቀቅ ይፈልጋል
በመላ አፍሪካ ርዕሰ ከተሞች መካከል፣ ለዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲና የጋራ አህጉራዊ ተቋማት ማዕከል በሆነችው ምድራችን፣ ታላቅ የሚዲያ መድረክ ማስተናገድ ታላቅ ኩራት ነው – የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት