ኤር ማሮክ የተባለው የሞሮኮ አየር መንገድ በዛሬው እለት እንዳስታወቀውም ከካዛብላንካ ወደ ዶሃ የሚደረጉ 30 በረራዎች ማክስኞ እና ረቡዕ ይደረጋሉ ብሏል፡፡
አየር መንገዱ ይህን ያደረገው ሞሮኮዊያን ዜጎችን ለማሰደስት እና ሀገሪቱ አፍሪካን ወክላ በአለም ዋንጫው ግማሽ ፍፃሜውን መቀላቀሏን ተከትሎ ስለመሆኑ ነው የተገለፀው፡፡
ሞሮኮ ፖርቹጋልን 1 ለ 0 በማሸነፍ ግማሽ ፍፃሜውን የተቀላቀለች ብቸኛዋ አፍሪካዊት ሀገር ስትሆን በመጪው ረቡዕ ፈረንሳይን እንደምትገጥም ሲጂቲኤን በዘገባው ጠቁሟል።
More Stories
ዳራማሎ ደንዳሾ ስፖርት ክለብ ባስኬት ቡናን በማሸነፍ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለፍፃሜ ያለፉ ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል
ስፖርት የወንድማማችነት እና የልማት መጠናከር አንዱ ማሳያ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ አስታወቀ