ኤር ማሮክ የተባለው የሞሮኮ አየር መንገድ በዛሬው እለት እንዳስታወቀውም ከካዛብላንካ ወደ ዶሃ የሚደረጉ 30 በረራዎች ማክስኞ እና ረቡዕ ይደረጋሉ ብሏል፡፡
አየር መንገዱ ይህን ያደረገው ሞሮኮዊያን ዜጎችን ለማሰደስት እና ሀገሪቱ አፍሪካን ወክላ በአለም ዋንጫው ግማሽ ፍፃሜውን መቀላቀሏን ተከትሎ ስለመሆኑ ነው የተገለፀው፡፡
ሞሮኮ ፖርቹጋልን 1 ለ 0 በማሸነፍ ግማሽ ፍፃሜውን የተቀላቀለች ብቸኛዋ አፍሪካዊት ሀገር ስትሆን በመጪው ረቡዕ ፈረንሳይን እንደምትገጥም ሲጂቲኤን በዘገባው ጠቁሟል።

More Stories
አትሌት ቢኒያም መላክ እና ውድነሽ ዓለሙ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የጎዳና ሩጫ ውድድርን አሸነፉ
የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የምስረታ በዓል የጎዳና ሩጫ ውድድር በሀዋሳ ከተማ በመካሄድ ላይ ነው
ማርከስ ራሽፎርድ ጉዳት አጋጥሞታል