ግንባታው የተከናወነው በአካባቢው ተወላጅ ባለሀብት አቶ ዳንኤልን ሱሊቶ እና በአካባቢው ማህበረሰብ ተሳትፎ መሆኑም ተገልጿል።
የአካባቢው ማህበረሰብ ከፍተኛ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት እጥረት የነበረበት ሲሆን ባለሀብቱና ማህበረሰቡ በጋራ በመሆን ባስገነቡት ይህ የጭንዳዊየ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት 6 ሺህ 500 የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተመላክቷል።
ዞኑ ከፍተኛ የከርሰ ምድር ውሃ ሀብት ባለቤት ሲሆን ማህበረሰብ፣ ባለሀብትና መንግስት እንዲሁም አጋር ድርጅቶች በመቀናጀት የውሃ አቅርቦት ተደራሽነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑም ተጠቁሟል።
በምረቃ ስነ-ስርዓቱ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውሃና መስኖ ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳዊት ኃይሉ፣ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የእምድብር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አቡነ ሉቃስ፣ የዞኑ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀል፣ የዞኑ ምክትል አፈጉባኤ አቶ ኸይሩ መሀመድ እና ሌሎች የዞኑና የወረዳው ከፍተኛ አመራሮች እና ባለሀብቶች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ እንዳልካቸው ደሳለኝ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ