ግንባታው የተከናወነው በአካባቢው ተወላጅ ባለሀብት አቶ ዳንኤልን ሱሊቶ እና በአካባቢው ማህበረሰብ ተሳትፎ መሆኑም ተገልጿል።
የአካባቢው ማህበረሰብ ከፍተኛ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት እጥረት የነበረበት ሲሆን ባለሀብቱና ማህበረሰቡ በጋራ በመሆን ባስገነቡት ይህ የጭንዳዊየ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት 6 ሺህ 500 የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተመላክቷል።
ዞኑ ከፍተኛ የከርሰ ምድር ውሃ ሀብት ባለቤት ሲሆን ማህበረሰብ፣ ባለሀብትና መንግስት እንዲሁም አጋር ድርጅቶች በመቀናጀት የውሃ አቅርቦት ተደራሽነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑም ተጠቁሟል።
በምረቃ ስነ-ስርዓቱ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውሃና መስኖ ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳዊት ኃይሉ፣ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የእምድብር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አቡነ ሉቃስ፣ የዞኑ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀል፣ የዞኑ ምክትል አፈጉባኤ አቶ ኸይሩ መሀመድ እና ሌሎች የዞኑና የወረዳው ከፍተኛ አመራሮች እና ባለሀብቶች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ እንዳልካቸው ደሳለኝ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ