ግንባታው የተከናወነው በአካባቢው ተወላጅ ባለሀብት አቶ ዳንኤልን ሱሊቶ እና በአካባቢው ማህበረሰብ ተሳትፎ መሆኑም ተገልጿል።
የአካባቢው ማህበረሰብ ከፍተኛ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት እጥረት የነበረበት ሲሆን ባለሀብቱና ማህበረሰቡ በጋራ በመሆን ባስገነቡት ይህ የጭንዳዊየ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት 6 ሺህ 500 የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተመላክቷል።
ዞኑ ከፍተኛ የከርሰ ምድር ውሃ ሀብት ባለቤት ሲሆን ማህበረሰብ፣ ባለሀብትና መንግስት እንዲሁም አጋር ድርጅቶች በመቀናጀት የውሃ አቅርቦት ተደራሽነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑም ተጠቁሟል።
በምረቃ ስነ-ስርዓቱ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውሃና መስኖ ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳዊት ኃይሉ፣ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የእምድብር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አቡነ ሉቃስ፣ የዞኑ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀል፣ የዞኑ ምክትል አፈጉባኤ አቶ ኸይሩ መሀመድ እና ሌሎች የዞኑና የወረዳው ከፍተኛ አመራሮች እና ባለሀብቶች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ እንዳልካቸው ደሳለኝ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ