የምክር ቤት አባላት ለህብረተሰቡ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በጋራ ሊሰሩ ይገባል – ዋና አፈ ጉባዔ ፀሀይ ወራሳ
ሀዋሳ፡ የካቲት 07/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የምክር ቤት አባላት ለህብረተሰቡ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በጋራ ሊሰሩ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባዔ ፀሀይ ወራሳ ገለጹ፡፡
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን፣ 4ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ነው።
የምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፀሀይ ወራሳ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮጵያ በለውጥ ሂደት ወቅት የገጠሟትን ፈተናዎች በጥበብ እያለፈች ነው ብለዋል።
በኢትዮጵያ በፖለቲካ፣ በማህበራዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ዘርፎች ስኬቶች እየተመዘገቡ ስለመሆኑ የጠቀሱት ወይዘሮ ፀሀይ፤ ስኬቱም የጠንካራ ፓርቲ እና መንግሥት ውጤት ነው በማለት ተናግረዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ልዩነትን በአንድነት ውስጥ ውበት አድርጎ እየተጓዘ ያለ ሲሆን ክልሉ በሀገሪቱ ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ላይ የራሱን አሻራ እያሳረፈ ነውም ብለዋል።
ነጣጣይ ትርክቶችን ወደጎን በመተው ለሀገር አንድነት በጋራ መስራት እንደሚገባም አሳስበዋል።
የህብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የምክር ቤት አባላት በጋራ መስራት እንዳለባቸው አመልክተዋል።
በበጀት አመቱ መጀመሪያ ላይ ፈፃሚ አካላት የዕቅድ ውል አስረው ወደ ስራ እንዲገቡ የተደረገ ሲሆን ምክር ቤቱ በቋሚ ኮሚቴዎች በኩል የቅርብ ክትትል መደረጉንም አፈ ጉባኤዋ አስረድተዋል።
ዘጋቢ፡ ጀማል የሱፍ

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ