ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) “ስለ ኢትዮጵያ” የተሰኘ ሃገራዊ የፓናል ውይይትና የፎቶግራፍ አውደ ርዕይ በቡታጅራ ከተማ አስጀመሩ
ሀዋሳ፡ የካቲት 06/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ያዘጋጀውን “ስለ ኢትዮጵያ” የተሰኘ ሃገራዊ የፓናል ውይይትና የፎቶ ግራፍ አውደ ርዕይ በቡታጅራ ከተማ አስጀምረዋል፡፡
በፎቶ ግራፍ አውደ ርዕዩ በክልሉ ያለውን የቱሪዝም፣ የኢኮኖሚና የግብርና ሃብቶች እንዲሁም ሃገር በቀል የዕርቀ ሰላም አቅጣጫዎችን የሚጠቁሙ ምስሎች ለዕይታ ቀርበዋል።
ውይይቱ “ሰላምና ኢኮኖሚ ስለ ኢትዮጵያ” በሚል እየተካሄደ ሲሆን ይህ መድረክ በሁለተኛው ምዕራፍ የመጀመሪያው መሆኑም ተጠቁሟል።
በመርሃ-ግብሩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ(ዶ/ር)፣ በኢፌዲሪ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክላስተር አስተባባሪዎች፣ የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ምህረተአብ እስራኤል
More Stories
በወላይታ ዞን ባለፉት 10 ወራት ውስጥ ህገ-ወጥ ንግድና ለመከላከል በተደረገው ክትትል 2 ሺህ 135 ነጋዴዎች ላይ የእርምት እርምጃ መውሰድ መቻሉን የዞኑ ንግድና ገበያ ልማት መመሪያ አስታወቀ
በ2017/18 የመኸር አዝመራ ከ4 መቶ ሺ ሄክታር በላይ ማሳን በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች መሸፈኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት የ10 ወራት አፈጻጸም እና የቀጣይ የክረምት ወራት ቅድመ ዝግጅት ግምገማ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ እያካሄደ ይገኛል