ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) “ስለ ኢትዮጵያ” የተሰኘ ሃገራዊ የፓናል ውይይትና የፎቶግራፍ አውደ ርዕይ በቡታጅራ ከተማ አስጀመሩ
ሀዋሳ፡ የካቲት 06/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ያዘጋጀውን “ስለ ኢትዮጵያ” የተሰኘ ሃገራዊ የፓናል ውይይትና የፎቶ ግራፍ አውደ ርዕይ በቡታጅራ ከተማ አስጀምረዋል፡፡
በፎቶ ግራፍ አውደ ርዕዩ በክልሉ ያለውን የቱሪዝም፣ የኢኮኖሚና የግብርና ሃብቶች እንዲሁም ሃገር በቀል የዕርቀ ሰላም አቅጣጫዎችን የሚጠቁሙ ምስሎች ለዕይታ ቀርበዋል።
ውይይቱ “ሰላምና ኢኮኖሚ ስለ ኢትዮጵያ” በሚል እየተካሄደ ሲሆን ይህ መድረክ በሁለተኛው ምዕራፍ የመጀመሪያው መሆኑም ተጠቁሟል።
በመርሃ-ግብሩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ(ዶ/ር)፣ በኢፌዲሪ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክላስተር አስተባባሪዎች፣ የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ምህረተአብ እስራኤል

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ