ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) “ስለ ኢትዮጵያ” የተሰኘ ሃገራዊ የፓናል ውይይትና የፎቶግራፍ አውደ ርዕይ በቡታጅራ ከተማ አስጀመሩ
ሀዋሳ፡ የካቲት 06/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ያዘጋጀውን “ስለ ኢትዮጵያ” የተሰኘ ሃገራዊ የፓናል ውይይትና የፎቶ ግራፍ አውደ ርዕይ በቡታጅራ ከተማ አስጀምረዋል፡፡
በፎቶ ግራፍ አውደ ርዕዩ በክልሉ ያለውን የቱሪዝም፣ የኢኮኖሚና የግብርና ሃብቶች እንዲሁም ሃገር በቀል የዕርቀ ሰላም አቅጣጫዎችን የሚጠቁሙ ምስሎች ለዕይታ ቀርበዋል።
ውይይቱ “ሰላምና ኢኮኖሚ ስለ ኢትዮጵያ” በሚል እየተካሄደ ሲሆን ይህ መድረክ በሁለተኛው ምዕራፍ የመጀመሪያው መሆኑም ተጠቁሟል።
በመርሃ-ግብሩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ(ዶ/ር)፣ በኢፌዲሪ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክላስተር አስተባባሪዎች፣ የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ምህረተአብ እስራኤል

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ