በዳውሮ ዞን ሎማ ቦሳ ወረዳ በተከሰተ ሰደድ እሳት ከሃያ ስድስት ሄክታር መሬት በላይ ምርቶች ሙሉ በሙሉ መውደሙን የወረዳ አስተዳደር አስታወቀ
በወረዳው አዲስ ቦዳሪ ቀበሌ ሾማ በተባለው አከባቢ የካቲት 04 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 6 ሰኣት ላይ የተከሰተው ሰደድ እሳት በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል፡፡
በቃጠሎው ምክንያት በሰው ሕይወት ላይ ጉዳት ባይደርስም ከ26 ሄክታር በላይ የሙዝ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ፣ እንድሁም የማልማት አቅም ያላቸው የውሃ ማስተላለፊያ ፕላስቲክ ቱቦ እና ሌሎች ምርት ሙሉ በሙሉ ውድመት መድረሱን የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ኢንጅነር ዘለቀ ሲሳይ አስታውቀዋል ።
የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ እና የፖሊስ አዛዥ እንዲሁም የወረዳው የሥራ ኃላፊዎች የጉዳቱን መጠን ተዘዋውሮ የጎበኘ ሲሆን፣ የሰደደ እሳት ከመስፋፋቱ በፊት በህብረተሰብ ተሳትፎ በቁጥጥር ስር ሊውል መቻሉን ተናግረዋል ።
ወቅቱ የበጋ ወቅትና ደረቃማ የአየር ሁኔታ መኖሩን ተከትሎ ከሰል ማክሰልና በእርሻ ማሳ ላይ የሚሎከስ እሳት በተፈጥሮ ሀብት ላይ እያደረሰ ካለው ተጽዕኖ ባሻገር የሰደድ እሳትን የሚያስከትል ስለሆነ ህብረተሰቡ ከሰል ከማክሰል እና እሳት ከመልቀቅ መቆጠብ እንዳለባቸው አስተዳዳሪው አሳስቧል።
የደረሰው ጉዳት አሳዛኝ ነው ሲል የገለጹት ዋና አስተዳዳሪው፥ የሰደድ እሳት መንስኤ በአግባቡ ተጣርቶ በድርጊቱ የተሳተፉ አካላት በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ እንደሚያደርግም አስታውቋል።
የጉዳቱ ሰላባ ከሆኑት መካከል አቶ አሰፋ ሶሬ እና አቶ አስረስ ሶሬ በሰጡት አስተያየት በተከሰተው አደጋ እጅግ ማዘናቸውን ገልጸው በብዙ ልፋትና በበርካታ ገንዘብ ወጥቶበት የለሙ በአንድ ደቂቃ አመድ መሆኑ በኢኮኖሚያቸው ላይ ትልቅ ጫና እንደሚፈጥር ገልፀዋል፡፡
ሆኖም የሰው ህይወትና ጉዳት ከመድረሱ በፊት እሳቱን መቆጣጠሩ ትልቅ ትርፍ መሆኑንን ተናግረዋል።
ዘጋቢ : አሸናፊ ግዛው – ከዋካ ጣቢያች

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ