በ2ኛው የብልጽግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ውሳኔዎች እና አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የአመራር የውይይት መድረክ በወልቂጤ ከተማ እየተካሔደ ነው

በ2ኛው የብልጽግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ውሳኔዎች እና አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የአመራር የውይይት መድረክ በወልቂጤ ከተማ እየተካሔደ ነው

ሀዋሳ፡ የካቲት 05/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ”መፍጠን እና መፍጠር ለጉባኤያችን ውሳኔዎች ስኬት” በሚል መሪ ሀሳብ በጉራጌ ዞን በ2ኛው የብልጽግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ውሳኔዎች እና አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የአመራር የውይይት መድረክ በወልቂጤ ከተማ እየተካሔደ ነው።

በሁሉም ዘርፍ ከቃል ወደ ባህል ለመሸጋገር እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ይበልጥ በማጠናከር ብልጽግናን ማረጋገጥ እንደሚገባ በመድረኩ ተገልጿል።።

የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ገብሬ ጋጌ፣ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የዞኑ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀል እና የዞኑ የስራ ኃላፊዎች በመድረኩ ተገኝተዋል።

ዘጋቢ፡ ሚፍታ ጀማል – ከወልቂጤ ጣቢያችን