በ2ኛው የብልጽግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ውሳኔዎች እና አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የአመራር የውይይት መድረክ በወልቂጤ ከተማ እየተካሔደ ነው
ሀዋሳ፡ የካቲት 05/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ”መፍጠን እና መፍጠር ለጉባኤያችን ውሳኔዎች ስኬት” በሚል መሪ ሀሳብ በጉራጌ ዞን በ2ኛው የብልጽግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ውሳኔዎች እና አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የአመራር የውይይት መድረክ በወልቂጤ ከተማ እየተካሔደ ነው።
በሁሉም ዘርፍ ከቃል ወደ ባህል ለመሸጋገር እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ይበልጥ በማጠናከር ብልጽግናን ማረጋገጥ እንደሚገባ በመድረኩ ተገልጿል።።
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ገብሬ ጋጌ፣ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የዞኑ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀል እና የዞኑ የስራ ኃላፊዎች በመድረኩ ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ሚፍታ ጀማል – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ