በ2ኛው የብልጽግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ውሳኔዎች እና አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የአመራር የውይይት መድረክ በወልቂጤ ከተማ እየተካሔደ ነው
ሀዋሳ፡ የካቲት 05/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ”መፍጠን እና መፍጠር ለጉባኤያችን ውሳኔዎች ስኬት” በሚል መሪ ሀሳብ በጉራጌ ዞን በ2ኛው የብልጽግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ውሳኔዎች እና አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የአመራር የውይይት መድረክ በወልቂጤ ከተማ እየተካሔደ ነው።
በሁሉም ዘርፍ ከቃል ወደ ባህል ለመሸጋገር እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ይበልጥ በማጠናከር ብልጽግናን ማረጋገጥ እንደሚገባ በመድረኩ ተገልጿል።።
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ገብሬ ጋጌ፣ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የዞኑ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀል እና የዞኑ የስራ ኃላፊዎች በመድረኩ ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ሚፍታ ጀማል – ከወልቂጤ ጣቢያችን
More Stories
በወላይታ ዞን ባለፉት 10 ወራት ውስጥ ህገ-ወጥ ንግድና ለመከላከል በተደረገው ክትትል 2 ሺህ 135 ነጋዴዎች ላይ የእርምት እርምጃ መውሰድ መቻሉን የዞኑ ንግድና ገበያ ልማት መመሪያ አስታወቀ
በ2017/18 የመኸር አዝመራ ከ4 መቶ ሺ ሄክታር በላይ ማሳን በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች መሸፈኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት የ10 ወራት አፈጻጸም እና የቀጣይ የክረምት ወራት ቅድመ ዝግጅት ግምገማ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ እያካሄደ ይገኛል