ለችግር የተጋለጡ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለመደገፍ የሚደረገው ጥረት ሊጠናከር እንደምገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፋይናንስ ቢሮ አሳሰበ
ሀዋሳ፡ ጥር 29/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ለችግር የተጋለጡ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለመደገፍ የሚደረገው ጥረት ሊጠናከር እንደምገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፋይናንስ ቢሮ ሀላፊ አቶ ተፈሪ አባቴ አሳስበዋል፡፡
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሠራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ በገቢ ማስገኛ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም እና ቀጣይ ዕቅድ ዙሪያ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በአርባ ምንጭ ከተማ የምክክር መድረክ አካሂዷል።
ቢሮው በ2016 ዓ.ም በክልሉ በ13 ዞኖች ለሚገኙ ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች 2 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በመመደብ ከኢኮኖሚያዊ ችግር ለማላቀቅ በትኩረት መሥራቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሠራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ዋኖ ዋሉሌ ተናግረዋል።
በቀጣይም በክልሉ ባሉ ስድስት ከተሞች ለተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን በመለየት በተለያዩ የሥራ ዘርፎች ለማሰማራት እና የገቢ ምንጭ እንዲፈጥሩ 5 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር መመደቡን ዶ/ር ዋኖ ገልጸዋል።
የክልሉ ፋይናንስ እና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ተፈሪ አባቴ እንዳሉት፤ በተለያዩ የኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ችግሮች የተጋለጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመምጣቱ መንግሥት በተለያዩ የገቢ ማስገኛ ዘርፎች ላይ በማሳተፍ ከችግር እንዲላቀቁ እየሠራ ነው፡፡
አክለውም ኃላፊው የተመደበው ሐብት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል በትኩረት ሊመራ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በመድረኩ ከክልሉ ከተለያዩ ዞኖች የተወጣጡ የሥራ ሀላፊዎች እና ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።
ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በሀድያ ዞን ሌሞ ወረዳ ከ5 ሺህ 9 መቶ በላይ ተማሪዎች ክልላዊና ሀገር አቀፍ ብሔራዊ ፈተና ለመውሰድ ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸው ተገለፀ
”ከተረጅነት ወደ ምርታማነት” በሚል መሪ ሃሳብ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በሀዋሳ ከተማ የውይይት መድረክ በመካሄድ ላይ ነው
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ