የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የፕላን መሠረተ ልማትና የመንግስት ሀብት አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚከታተላቸውን ተቋማት ሪፖርት እያደመጠ ነው
ሀዋሳ: ጥር 28/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የፕላን መሠረተ ልማትና የመንግስት ሀብት አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚከታተላቸውን ተቋማት የ2017 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ሪፖርት እየገመገመ ነው።
የክልሉ ምክር ቤት የፕላን መሠረተ ልማትና የመንግስት ሀብት አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፥ የዘርፉን ተቋማት የ2017 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እየገመገመ ነው።
ቋሚ ኮሚቴው በሚከታተላች ተቋማት በ2017 መጀመሪያ ግማሽ አመት የተከናወኑ የልማት ስራዎችን በቀረበው ሪፖርት ላይ አስተያየት፣ ጥያቄዎችንና ግብረ መልሶችን እየሰጠ ነው።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የፕላን መሠረተ ልማትና የመንግስት ሀብት አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ እንቁ ዮሐንስ ጨምሮ የቋሚ ኮሚቴ አባላትና የተቋማቱ የቢሮ ኃላፊዎች እንዲሁም የማኔጅመንት አባላት እየተሳተፉ ነው።
ዘጋቢ: ስላባት ባህሪው

More Stories
የሰራተኞች የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር ብዙዎችን የቤት ባለቤት ማድረጉ ተገለጸ
በሁሉም ዘርፎች እንደሀገር አመርቂ ውጤቶች እየተዘመገቡ ነው – የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርዓትን በማዘመን የመረጃ ታማኝነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ