የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የማህበራዊ ዘርፍ ተቋማትን የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ማካሄድ ጀመረ
ሀዋሳ: ጥር 28/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የማህበራዊ ዘርፍ ተቋማትን የ2017 ዓ.ም የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እያካሔደ ነው።
የክልሉ ምክር ቤት የሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴም የክልሉን ጤና ቢሮ እንዲሁም የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ የ2017 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም መገምገም ጀምሯል።
በዚህም ቋሚ ኮሚቴው የተቋማቱን የግማሽ ዓመት ሪፖርት በማድመጥ ጥያቄዎችንና ግብረ መልሶችን ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።
በግማሽ ዓመቱ የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርትም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ እመቤት ወንድሙን ጨምሮ የቋሚ ኮሚቴ አባላትና የተቋማቱ የቢሮ ኃላፊዎች እንዲሁም የማናጅመንት አካላት ተሳታፊ እየሆኑ ይገኛሉ።
ዘጋቢ: ቃልአብ ጸጋዬ

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ