የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የማህበራዊ ዘርፍ ተቋማትን የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ማካሄድ ጀመረ
ሀዋሳ: ጥር 28/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የማህበራዊ ዘርፍ ተቋማትን የ2017 ዓ.ም የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እያካሔደ ነው።
የክልሉ ምክር ቤት የሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴም የክልሉን ጤና ቢሮ እንዲሁም የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ የ2017 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም መገምገም ጀምሯል።
በዚህም ቋሚ ኮሚቴው የተቋማቱን የግማሽ ዓመት ሪፖርት በማድመጥ ጥያቄዎችንና ግብረ መልሶችን ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።
በግማሽ ዓመቱ የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርትም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ እመቤት ወንድሙን ጨምሮ የቋሚ ኮሚቴ አባላትና የተቋማቱ የቢሮ ኃላፊዎች እንዲሁም የማናጅመንት አካላት ተሳታፊ እየሆኑ ይገኛሉ።
ዘጋቢ: ቃልአብ ጸጋዬ
More Stories
ከመግፋፋት በመውጣት የመደመር ዕሳቤን በማጎልበት በህዝቦች መካከል ያሉ ወንድማማችነትን ማሳደግ እንደሚገባ የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድርና የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ አባል አቶ ኦርዲን በድሪ ተናገሩ
የዲላ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ መስክ ያስተማራቸውን 518 ተማሪዎችን አስመርቋል፡፡
ውጤታማ የሆነ ስራ የሰራ አካባቢ ተጨማሪ ፕሮጀክት የማግኘት ዕድል አለው – ሚ/ር ዴኤታ የትምጌታ አስራት