የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የማህበራዊ ዘርፍ ተቋማትን የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ማካሄድ ጀመረ
ሀዋሳ: ጥር 28/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የማህበራዊ ዘርፍ ተቋማትን የ2017 ዓ.ም የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እያካሔደ ነው።
የክልሉ ምክር ቤት የሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴም የክልሉን ጤና ቢሮ እንዲሁም የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ የ2017 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም መገምገም ጀምሯል።
በዚህም ቋሚ ኮሚቴው የተቋማቱን የግማሽ ዓመት ሪፖርት በማድመጥ ጥያቄዎችንና ግብረ መልሶችን ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።
በግማሽ ዓመቱ የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርትም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ እመቤት ወንድሙን ጨምሮ የቋሚ ኮሚቴ አባላትና የተቋማቱ የቢሮ ኃላፊዎች እንዲሁም የማናጅመንት አካላት ተሳታፊ እየሆኑ ይገኛሉ።
ዘጋቢ: ቃልአብ ጸጋዬ
More Stories
ስፖርት በአንድ አካባቢ የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ከማቀራረቡም በተጨማሪም ለአንድ አካባቢ ሰላም መስፈን ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት የጉራጌ ዞን አስተዳደር ገለጸ
አምረፍ ሄልዝ አፍሪካ ግብረ ሰናይ ድርጅት ለበርካታ ዓመታት የጤናውን ዘርፍ በመደገፍ የማይተካ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ
ከእርሻ መሬት መጠቀሚያ ግብር 20 ሚሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ዞን የጎምቦራ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ ቤት አስታወቀ