በክልሉ ከ240 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የሚገነቡ መናኸሪያዎች ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ አስታወቀ
መናኸሪያዎቹ በ2 ወር ባልበለጠ ጊዜ ተጠናቀው ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጡ እንደሚሰራም ተገልጿል።
በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋጅዮ ሳፒ እንደገለፁት፤ በክልሉ ባለፉት 6 ወራት በርካታ የመሠረተ ልማት ተግባራት ሲከናወኑ መቆየታቸውን ገልፀዋል።
የትራንስፖርት መሠረተ ልማትን ለማሳለጥ የክልል መንግስት ትኩረት ሰጥቶ ከሚሰራቸው ተግባራት መካከል በቀድሞ የደቡብ ክልል መንግስት የተጀመሩ የመንገድ፣ የድልድይና የመናኸሪያ ግንባታዎች ተጠቃሾች መሆናቸውን ኃላፊው አስረድተዋል።
እነዚህም የታረጫ 99፣ የቦንጋ 94 እና የሚዛን 56 በአጠቃላይ ከ249 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የመናኸሪያዎች ግንባታ እየተሰሩ እንደሚገኝ አቶ ፋጅዮ ተናግረዋል።
ከ3ቱም መናኸሪያዎች የታርጫና የሚዛን በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቁ የገለፁት የቢሮ ኃላፊው፤ በተለያዩ ምክንያቶች የቦንጋ ሊቆይ የሚችል ቢሆንም ግንባታው በዚህ ዓመት ይጠናቀቃል ብለዋል።
ግንባታዎቹ በቀድሞ የደቡብ ክልል ተጀምረው ያልተጠናቀቁ በመሆናቸው የቢሮ ኃላፊዎች ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጋር እስከ ቦታው ድርስ በመጎብኘት ችግሮቹ እንዲፈቱ ሲደረግ መቆየቱን አቶ ፋጅዮ ገልጸዋል።
በተለይም የሚዛን መናኸሪያ ቦታውን ምቹ ለማድረግ ኮረት እየተደፋ እንደሚገኝና የመውጫ እና የመግቢያ ቦታዎች የመለየት ሥራ ተሰርተው በቅርቡ እንደሚጠናቀቅ የቢሮ ኃላፊው ተናግረዋል።
መናኸሪያዎቹ አገልግሎት መስጠት በሚጀምሩበት ወቅት ከትራንስፖርት ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ መጨናነቆች በእጅጉ እንደሚቀንሱም አቶ ፋጅዮ አብራርተዋል።
ዘጋቢ፡ አብዲሳ ዮናስ – ከሚዛን ጣቢያችን

 
                 
                                         
                                         
                                         
                                        
More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ