በዞኑ “የአፈር ሀብታችን ለብልጽግናችን” በሚል መሪ ቃል ከጥር 22 ጀምሮ ለተከታታይ 45 ቀናት በዞኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ እንደሚካሄድም ተገልጿል።
በዞኑ ከጪ ወረዳ የቺ ገዳ ንዑስ ተፋሰስ ዞናዊ በሆነው የማስጀመሪያ መርሀ ግብር የተገኙ አርሶአደሮች እንደሚሉት ባለፉት ዓመታት በለሙ የአፈርና ጥበቃ ሥራዎች አካባቢያቸው ተጠቃሚ መሆን ችሏል።
በተለይ ቀበሌያቸው በአፈር አሲዳማነት የተጠቃ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የሚታየውን ችግር ለመፍታት የአፈርና ውኃ ጥበቃ ተግባርን በትጋት እንደሚወጡ ተናግረዋል።
የዳውሮ ዞን ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ በተላ በየነ እንደገለጹት በዞኑ የተፈጥሮ ሀብት መመናመን እና የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል ከመቼውም ጊዜ በላይ የአፈርና ውኃ ጥበቃ ሥራዎች በትኩረት እየተከናወኑ ይገኛሉ።
የዘንድሮ 2017 ዓ.ም የተቀናጀ የማህበረሰብ ተፋሰስ ልማት የተፈጥሮ ሀብት መጠበቅ፣ ማልማትና በማቀናጀት ጥቅም ላይ ለማዋል በዘንድሮ የተፋሰስ ልማት ከ4 መቶ 8 ሺህ 8 መቶ 76 በላይ የማህበረሰብ ክፍሎችም በተግባሩ እየተሳተፉ ይገኛሉ ።
ለዕቅዱ መሳካት አስፈላጊዉ የዝግጅት ሥራዎች ከታህሣሥ አጋማሽ ጀምሮ የተከናወኑ ሲሆን ሥልጠና መስጠት፣ የልየታና የዲዛይን ስራ እንዲሁም የሰዉ ኃይልም ይሁን የመሳሪያ ልየታ በተገቢዉ መከናወኑንም አስረድተዋል።
በዳዉሮ ዞን ከጪ ወረዳ በማስጀመሪያ መርሀግብር የተገኙ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ተሳትፏዊ ግብርናና የአየር ንብረት ሽግግር ፕሮግራም ሥራ አስኪያጅ አቶ ታመነ ተስፋዬ በበኩላቸው ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ ካስገኘው ውጤት መነሻ በክልሉ 2 መቶ 25 ሺህ ሄክታር ማሣ በተለዩ 1 ሺህ 1 መቶ 90 ንዑስ ተፋሰሶች እንደሚለሙ ገልጸዋል።
በዳዉሮ ዞንም ወደ 40 ሄክታር የሚጠጋ ማሣ በነባር 3 መቶ 57 ንዑስ ተፋሰሶች እና 50 አዳዲስ ንዑስ ተፋሰሶች የሚለማ ሲሆን ከዘርፉ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሥነ ሕይወታዊና የጥበቃ ሥራዎች በትኩረት ሊሠራ እንደሚገባም አስረድተዋል።
ዘጋቢ ፡መሣይ መሠለ-ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ