የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን የተቋሙን የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ከባለድርሻ አካላት ጋር እየገመገመ ይገኛል
ሀዋሳ፡ ጥር 22/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን የተቋሙን የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ከባለድርሻ አካላት ጋር በወልቂጤ ከተማ እየገመገመ ነው።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ምስጋናው ማቲዮስ፤ መድረኩ በበጀት አመቱ በመጀመሪያው ግማሽ አመት የነበሩ ጠንካራ ጎኖችን አጠናክሮ ለማስቀጠልና ውስንነቶችን ለመቅረፍ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በተለይም በዘርፉ የተያዙ ግቦችን ለማሳካት የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቅንጅት ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል።
በመድረኩ አሁን ላይ የባለስልጣኑ እና የዲስትሪክቶች የ2017 በጀት አመት የግማሽ አመት አፈፃፀም ሪፖርት እየቀረበ ይገኛል፡፡
በመድረኩ ላይ የክልሉ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ምስጋናው ማቲዮስን ጨምሮ የዲስትሪክቶች የስራ ሃላፊዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ፡፡
ዘጋቢ፡ ጅላሉ ፈድሉ – ከወልቂጤ ጣቢያችን
More Stories
በወላይታ ዞን ባለፉት 10 ወራት ውስጥ ህገ-ወጥ ንግድና ለመከላከል በተደረገው ክትትል 2 ሺህ 135 ነጋዴዎች ላይ የእርምት እርምጃ መውሰድ መቻሉን የዞኑ ንግድና ገበያ ልማት መመሪያ አስታወቀ
በ2017/18 የመኸር አዝመራ ከ4 መቶ ሺ ሄክታር በላይ ማሳን በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች መሸፈኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት የ10 ወራት አፈጻጸም እና የቀጣይ የክረምት ወራት ቅድመ ዝግጅት ግምገማ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ እያካሄደ ይገኛል