የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን የተቋሙን የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ከባለድርሻ አካላት ጋር እየገመገመ ይገኛል
ሀዋሳ፡ ጥር 22/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን የተቋሙን የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ከባለድርሻ አካላት ጋር በወልቂጤ ከተማ እየገመገመ ነው።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ምስጋናው ማቲዮስ፤ መድረኩ በበጀት አመቱ በመጀመሪያው ግማሽ አመት የነበሩ ጠንካራ ጎኖችን አጠናክሮ ለማስቀጠልና ውስንነቶችን ለመቅረፍ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በተለይም በዘርፉ የተያዙ ግቦችን ለማሳካት የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቅንጅት ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል።
በመድረኩ አሁን ላይ የባለስልጣኑ እና የዲስትሪክቶች የ2017 በጀት አመት የግማሽ አመት አፈፃፀም ሪፖርት እየቀረበ ይገኛል፡፡
በመድረኩ ላይ የክልሉ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ምስጋናው ማቲዮስን ጨምሮ የዲስትሪክቶች የስራ ሃላፊዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ፡፡
ዘጋቢ፡ ጅላሉ ፈድሉ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ