በቤንች ሸኮ ዞን የዘንድሮው የተፋሰስ ልማት ስራ በይፋ ተጀመረ
ሀዋሳ፡ ጥር 22/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በቤንች ሸኮ ዞን የዘንድሮው የተፋሰስ ልማት ስራ በሼይ ቤንች ወረዳ ማዝ ቀበሌ በይፋ ተጀምሯል።
በክልሉ በሚገኙ ሁሉም ዞኖች የተፈሰስ ልማት ስራው በይፋ የተጀመረ ሲሆን በቤንች ሸኮ ዞን ሼይ ቤንች ወረዳ ማዝ ቀበሌ የአካባቢው ማህበረሰብ እንዲሁም የክልልና የዞን አመራሮች በተገኙበት የተፋሰስ ልማት ስራ ተከናውኗል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ሃላፊው አቶ መስፍን መንገሻ እንደተናገሩት፤ የአፈር ሀብታችንን መጠበቅ ተፈጥሮን መንከባከብና የውሀ ሀብታችንን መጠበቅ በመሆኑ ዘንድሮ በልዩ ትኩረት እየተሰራ ነው።
የተፋሰስ ልማት ለበርካታ አመታት እየተሰራ የቆየና በህዝቡ ውስጥ ባህል ሆኖ የቆየ ተግባር መሆኑን ገልጸው፤ ዘንድሮ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራን ብቻ ሳይሆን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው አትክልትና ፍራፍሬዎች፣ የመኖ ሳርና መሰል ስራዎችን እንሰራለን ብለዋል።
የዞኑ ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን ጉብላ እንደተናገሩት፤ በዞኑ በ96 ንዑስ ተፋሰሶች 34ሺ 480 ሄክታር መሬት ላይ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ ይሰራል።
የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራችንን መስራት የአፈር ለምነትን በማስጠበቅ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ያግዛል ብለዋል።
በስራው የተሳተፉ አርሶ አደሮችም የተፋሰስ ልማቱ ለምርታማነት ዕድገት ከሚኖረው አስተዋጽኦ በተጨማሪ የመሬት መንሸራተትን በመከላከል ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል
በዞኑ ለ45 ቀናት በሚቆየው የአካባቢ ጥበቃ ስራ 34ሺህ ሄክታር በላይ መሬት የሚሸፍን 96 ተፋሰሶች ለአካባቢ ጥበቃ ስራ ተለይተዋል።
ዘጋቢ፡ ጦያር ይማም – ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ