በዳሎል ማዕከላዊ ዕዝ ስር የ101ኛ ሕዳሴ ኮር የሠራዊት አባላት በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌያት በድንገተኛ የመሬት መንሸራተት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኞች መልሶ ማቋቋሚያ 820 ሺህ 400 ብር ድጋፍ አደረጉ
ድጋፉ በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኮሩ ምክትል አዛዥ ኮሎኔል ኢያሱ ሀብቱ ገልጸዋል።
ኮሎኔል ኢያሱ ሀብቱ፤ አደጋው በደረሰበት ወቅት በተለያዩ ሀገራዊ ተልዕኮዎች ላይ እንደነበሩ ገልጸዉ የዕዙ ሰራዊት አባላት አሁንም ሰላም ከማስከበር ስራው ጎን ለጎን ህብረተሰቡን በተለያዩ መንገዶች እየደገፉ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ድጋፉን የተረከቡት የጎፋ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ታደለ ያዕቆብ፤ የሀገር መከላከያ ሠራዊት የኢትዮጵያ ሉአላዊነትና ዳር ድንበር እንዲከበር የሕይወት መስዋዕትነት እየከፈለ የኖረ የሀገር አለኝታ መሆኑን ተናግረዋል።
የኮሩ አመራሮችና አባላት ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን በመወጣት በአደጋው የተፈናቀሉ የኅብረተሰብ ክፍሎችን በዘላቂነት ለማቋቋም ላደረጉት የገንዘብ ድጋፍ በዞኑ መንግስትና በተጎጂ ቤተሰቦች ስም አመስግነዋል።
ዘጋቢ: አወል ከድር – ከሳውላ ጣቢያችን
በዳሎል ማዕከላዊ ዕዝ ስር የ101ኛ ሕዳሴ ኮር የሠራዊት አባላት በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌያት በድንገተኛ የመሬት መንሸራተት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኞች መልሶ ማቋቋሚያ 820 ሺህ 400 ብር ድጋፍ አደረጉ

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ