የተፈጥሮ ሃብት የሆነውን መሬትን በአግባቡ በመጠበቅ ምርታማነትን በማሳደግ ብልፅግናን ማረጋገጥ ይገባል – የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ደንና አካባቢ ጥበቃ ቢሮ
የተፈጥሮ ሃብት የሆነውን መሬትን በአግባቡ በመጠበቅ ምርታማነትን በማሳደግ ብልፅግናን ማረጋገጥ እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ደንና አካባቢ ጥበቃ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብርሃም መጫ ገለፁ፡፡
ሃላፊው ይህን የገለፁት በክልሉ በቀቤና ልዩ ወረዳ የ2017 የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራ እወጃ በልዩ ወረዳው በሩሙጋ ቀበሌ በተካሄደበት ወቅት ነው።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ደንና አካባቢ ጥበቃ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብርሃም መጫ በመርሃ-ግብሩ ላይ እንደገለፁት፤ ሀገራችንን ከድህነት ማውጣት የሚቻለው የተፈጥሮ ሃብት የሆኑትን መሬት፣ ውሃ፣ የሰው ሃብት እና ጊዜን በአግባቡ አቀናጅቶ መጠቀም ሲቻል ነው፡፡
የቀቤና ልዩ ወረዳ ለግብርና ስራ ምቹ ስነ-ምህዳርና የአየር ፀባይ ያለው ነው ያሉት አቶ አብረሃም እየተሰራ ያለውን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራ በስነ-ህይወታዊ ስራዎች ማልማት እንደሚገባም ገልፀዋል፡፡
የቀቤና ልዩ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አብድልሽኩር ደሊል በበኩላቸው፤ በዘንድሮው የተፋሰስ ልማት ስራ በልዩ ወረዳው በ23 ንኡስ ተፋሰሶች 4ሺህ 200 ሄክታር መሬት ለማልማት ግብ ተይዞ ወደ ተግባር መገባቱን አስረድተዋል፡፡
ለዚህም አስፈለጊውን የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በማጠናቀቅ ስራውን በይፋ በሩሙጋ ቀበሌ ማስጀመር መቻሉን አቶ አብድልሽኩር ገልፀዋል።
በተፋሰስ ልማት ስራው ከ25 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚሳተፉ ኃላፊው ተናግረዋል፡፡
አሁን ላይ የልዩ ወረዳው አርሶ አደር ለተፋሰስ ልማት ስራ ያለው ተነሳሽነትና ፍላጎት ከፍተኛ መሆኑን ያስታወቁት ደግሞ የልዩ ወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ምክትልና የተፈጥሮ ሃብት ልማት ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ረሻድ አስፋው ናቸው፡፡
ባለፉት አመታት በተከናወኑ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች የአርሶ አደሩ ምርትና ምርታማነት ማሳደግ መቻሉንም አስረድተዋል፡፡
የተፋሰስ ልማት ስራ ምንጮችና ወንዞች እንዲጎለብቱ ያስቻለ ከመሆኑም ባሻገር የተጎሳቆሉ መሬቶች ማገገማቸውና ምርታማነታቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን የልዩ ወረዳው አርሶ አደሮች ተናግረዋል፡፡
በመሆኑም በዘንድሮው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ውጤታማነት በትኩረት እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡
ዘጋቢ፡ እቴነሽ ቲሬቦ – ከወልቂጤ ጣቢያችን
More Stories
ቆሻሻን በአግባቡ በማስወገድ ከተማዋ ፅዱና ውብ እንድትሆን የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ነው – የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በቋሚነት የሚደገፉበት ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የቡርጂ ዞን አስተዳደር አስታወቀ
“አንድ ሰው ወደዚህች ምድር ሲመጣ እንዲሰራ የተፈቀደለትና የሚጠበቅበት ነገር አለ” – ታደሰ ገብሬ /ጃክሰን/