አመራሩ በቀጣዮቹ 6 ወራት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለቅሞ መፍታት እንዳለበት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ(ዶ/ር) አሳሰቡ
የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት ባካሄደዉ 22ኛ መደበኛ ጉባኤ የ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ላይ ተወያይቶ አጽድቋል።
ለ2 ቀናት በሆሳዕና ከተማ በተካሄደዉ የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት 22ኛ መደበኛ ጉባኤ፤ የክልሉ አስፈፃሚ አካላት የ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ቀርቦ ሰፊ ዉይይት ተደርጎበታል።
በበጀት ዓመቱ መጀመሪያ፤ በዕቅድ ላይ በቂ ዝግጅት በማድረግ አዳዲስ ሀሳቦች እንዲካተቱ መደረጉ በጥንካሬ የሚታይ መሆኑን የገለፁት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ(ዶ/ር)፣ በፈፃሚ ዝግጅት ላይ የነበረዉ ተግባርም በጥንካሬ የሚወሰድ እንደሆነ ጠቅሰዋል።
በተግባር ምዕራፍ ስራን ቆጥሮ መዉሰድ፣ ዉጤትን እየገመገሙ መሄድ፣ ጊዜን ለስራ ብቻ ማዋል እንዲሁም የህዝብን ተጠቃሚነት እየገመገሙ ተሳትፎን ማሳደግ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።
አመራሩ ከደባል አጀንዳ በመዉጣት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ነቅሶ መፍታት የቀጣይ 6 ወራት የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን በማጠቃለያ ሀሳባቸዉ ያሳሰቡት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር፤ አገልግሎትን ከእጅ መንሻ በፀዳ መልኩ በስታንዳርድ መስጠት ይገባል ብለዋል።
በከተሞች የማህበር ቤት ግንባታን ወደ ስራ ማስገባት፣ የወጣቶችና ሴቶችን ተሳትፎ ማሳደግ፣ ምርታማነትን በማሳደግ የኑሮ ዉድነትን ማረጋጋት የቀጣይ 6 ወራት የትኩረት አቅጣጫዎች መሆናቸውን የጠቀሱት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ የገቢና ስራ ዕድል ፈጠራ ስራዎችም በቀሪ ወራት በትኩረት መመራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የክልሉን ሰላም ለማስጠበቅ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረዉ መቀጠል እንዳለባቸዉ ያሳሰቡት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ የቀሩ ተግባራትም እልባት ማግኘት እንዳለባቸዉ አስገንዝበዋል።
መስተዳድር ምክር ቤቱ የ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀሙ ላይ ተወያይቶ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።
ዘጋቢ፡ ድልነሳው ታደሰ

More Stories
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ