በጉራጌ ዞን ባለፋት ስድስት ወራት ለውጭ ገበያ ከቀረቡ ምርቶች ከ11 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የዞኑ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ገለፀ
ይህ የተገለፀው መምሪያው የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማና የ2ኛ ግማሽ በጀት ዓመት የዜጎች ቻርተር የውይይት መድረክ በወልቂጤ ከተማ ባካሄደበት ወቅት ነው።
መድረኩን በንግግር የከፈቱት የጉራጌ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ መላኩ ብርሀኔ እንዳሉት፤ በጉራጌ ዞን ባለፋት ስድስት ወራት ለውጭ ገበያ ከቀረቡ ምርቶች ከ11 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል።
በስድስት ወር ውስጥ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ እድሳት ለማድረግ በተሰራዉ ስራ ከ11 ሺህ በላይ ነጋዴዎችን መመዝገብ መቻሉን ገልፀው፤ ከነዚህ ዉስጥ 8 ሺህ 8 መቶ ኦንላይን ማስገባት መቻሉም ተናግረዋል።
የመምሪያው ሀላፊ አክለውም የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት ነባር የሸማች ማህበራትን በማጠናከርና አዳዲስ በማደራጀት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።
አቶ ነጋ አስፋው፣ በለጠ ሳሌና ኸይሪያ ጀማል የመድረኩ ተሳታፊዎች ሲሆኑ የሰንበት ገበያዎችን በማጠናከር የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት ጥረት እያደረግን ነው ብለዋል።
በተጨማሪም ድጋፍ ለሚሹ የማህበረሰብ ክፍሎች የተለያዩ ድጋፍ ማድረጋቸውን ገልፀዋል።
ነባር ንግድ ፍቃድ በማሳደስ፣ አዲስ ንግድ ፍቃድ በኦንላይን በመስጠት ላይ መሆናቸውንም ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ አስፍር ሙህዲን – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ