በጉራጌ ዞን ባለፋት ስድስት ወራት ለውጭ ገበያ ከቀረቡ ምርቶች ከ11 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የዞኑ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ገለፀ
ይህ የተገለፀው መምሪያው የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማና የ2ኛ ግማሽ በጀት ዓመት የዜጎች ቻርተር የውይይት መድረክ በወልቂጤ ከተማ ባካሄደበት ወቅት ነው።
መድረኩን በንግግር የከፈቱት የጉራጌ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ መላኩ ብርሀኔ እንዳሉት፤ በጉራጌ ዞን ባለፋት ስድስት ወራት ለውጭ ገበያ ከቀረቡ ምርቶች ከ11 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል።
በስድስት ወር ውስጥ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ እድሳት ለማድረግ በተሰራዉ ስራ ከ11 ሺህ በላይ ነጋዴዎችን መመዝገብ መቻሉን ገልፀው፤ ከነዚህ ዉስጥ 8 ሺህ 8 መቶ ኦንላይን ማስገባት መቻሉም ተናግረዋል።
የመምሪያው ሀላፊ አክለውም የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት ነባር የሸማች ማህበራትን በማጠናከርና አዳዲስ በማደራጀት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።
አቶ ነጋ አስፋው፣ በለጠ ሳሌና ኸይሪያ ጀማል የመድረኩ ተሳታፊዎች ሲሆኑ የሰንበት ገበያዎችን በማጠናከር የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት ጥረት እያደረግን ነው ብለዋል።
በተጨማሪም ድጋፍ ለሚሹ የማህበረሰብ ክፍሎች የተለያዩ ድጋፍ ማድረጋቸውን ገልፀዋል።
ነባር ንግድ ፍቃድ በማሳደስ፣ አዲስ ንግድ ፍቃድ በኦንላይን በመስጠት ላይ መሆናቸውንም ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ አስፍር ሙህዲን – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ