ጀፎረ ዘመን የቀደመ ባህላዊ የምህንድስና ጥበብ አሻራ” በሚል መርህ የተዘጋጀ ዞናዊ የገጠር ኮሪደር ልማት ማስጀመሪያ መድረክ በጉራጌ ዞን እኖር ወረዳ ወሽዘውያር ቀበሌ በውቡ ኧሴዳሜ ጀፎረ ተካሄደ
“ጀፎረ ዘመንን የቀደመ ባህላዊ የምህንድስና ጥበብ አሻራ” በሚል መርህ የተዘጋጀ ዞናዊ የገጠር ኮሪደር ልማት ማስጀመሪያ መድረክ በጉራጌ ዞን እኖር ወረዳ ወሽዘውያር ቀበሌ በውቡ ኧሴዳሜ ጀፎረ ተካሄዷል ።
እንደ ሀገር የተጀመረው የገጠር ኮሪደር ልማት አጠናክሮ በማስቀጠል የጉራጌ ጀፎረን ማስተዋወቅ እና ለትውልድ ማስተላለፍ እንደሚያስፈልግ ተመላክቷል።
በመድረኩ ላይ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ ፣ የዞኑ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀልን ጨምሮ የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር የስራ ኃላፊዎች፣ ከወልቂጤ ዩኒቨርስቲ፣ ከጉራጌ ልማትና ባህል ማህበር ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ ፡ተረፈ ሀብቴ-ከወልቂጤ ጣቢያችን
More Stories
ቆሻሻን በአግባቡ በማስወገድ ከተማዋ ፅዱና ውብ እንድትሆን የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ነው – የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በቋሚነት የሚደገፉበት ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የቡርጂ ዞን አስተዳደር አስታወቀ
“አንድ ሰው ወደዚህች ምድር ሲመጣ እንዲሰራ የተፈቀደለትና የሚጠበቅበት ነገር አለ” – ታደሰ ገብሬ /ጃክሰን/