ጀፎረ ዘመን የቀደመ ባህላዊ የምህንድስና ጥበብ አሻራ” በሚል መርህ የተዘጋጀ ዞናዊ የገጠር ኮሪደር ልማት ማስጀመሪያ መድረክ በጉራጌ ዞን እኖር ወረዳ ወሽዘውያር ቀበሌ በውቡ ኧሴዳሜ ጀፎረ ተካሄደ
“ጀፎረ ዘመንን የቀደመ ባህላዊ የምህንድስና ጥበብ አሻራ” በሚል መርህ የተዘጋጀ ዞናዊ የገጠር ኮሪደር ልማት ማስጀመሪያ መድረክ በጉራጌ ዞን እኖር ወረዳ ወሽዘውያር ቀበሌ በውቡ ኧሴዳሜ ጀፎረ ተካሄዷል ።
እንደ ሀገር የተጀመረው የገጠር ኮሪደር ልማት አጠናክሮ በማስቀጠል የጉራጌ ጀፎረን ማስተዋወቅ እና ለትውልድ ማስተላለፍ እንደሚያስፈልግ ተመላክቷል።
በመድረኩ ላይ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ ፣ የዞኑ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀልን ጨምሮ የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር የስራ ኃላፊዎች፣ ከወልቂጤ ዩኒቨርስቲ፣ ከጉራጌ ልማትና ባህል ማህበር ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ ፡ተረፈ ሀብቴ-ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ