ጀፎረ ዘመን የቀደመ ባህላዊ የምህንድስና ጥበብ አሻራ” በሚል መርህ የተዘጋጀ ዞናዊ የገጠር ኮሪደር ልማት ማስጀመሪያ መድረክ በጉራጌ ዞን እኖር ወረዳ ወሽዘውያር ቀበሌ በውቡ ኧሴዳሜ ጀፎረ ተካሄደ
“ጀፎረ ዘመንን የቀደመ ባህላዊ የምህንድስና ጥበብ አሻራ” በሚል መርህ የተዘጋጀ ዞናዊ የገጠር ኮሪደር ልማት ማስጀመሪያ መድረክ በጉራጌ ዞን እኖር ወረዳ ወሽዘውያር ቀበሌ በውቡ ኧሴዳሜ ጀፎረ ተካሄዷል ።
እንደ ሀገር የተጀመረው የገጠር ኮሪደር ልማት አጠናክሮ በማስቀጠል የጉራጌ ጀፎረን ማስተዋወቅ እና ለትውልድ ማስተላለፍ እንደሚያስፈልግ ተመላክቷል።
በመድረኩ ላይ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ ፣ የዞኑ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀልን ጨምሮ የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር የስራ ኃላፊዎች፣ ከወልቂጤ ዩኒቨርስቲ፣ ከጉራጌ ልማትና ባህል ማህበር ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ ፡ተረፈ ሀብቴ-ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ