የጤና ሥራን ለማሳለጥ መረጃ ህይወት መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ እንዳሻው ሽብሩ ተናገሩ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ በክልሉ ላሉ ዞኖች አምቡላንሶች፣ ሞተር ብስክሌቶች፣ ኮምፒውተሮች እና ሌሎች ቁሳቁሶችን ድጋፍ አድርጓል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሰት ጤና ቢሮ ከኢፌዲሪ ጤና ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት ያገኛቸውን አምቡላንሶች፣ የሞተር ብስክሌቶች፣ ኮምፒውተሮች እና ሌሎች ቁሳቁሶችን ለክልሉ ዞኖች ድጋፍና ርክክብ ማድረጊያ መርሀ-ግብር አካሂዷል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ እንደሻው ሽብሩ፤ ክልሉ አዲስ እንደመሆኑ መጠን የተለያዩ በክልሉ ያሉ ዞኖች በርካታ የግብዓት እጥረት ያሉባቸው እንደመሆኑ አምቡላንስ፣ ሞተር ሳይክሎችና ኮምፒውተሮች ድጋፍ መደረጋቸውን አንስተዋል።
የጤናውን ሥራ ለማሳለጥ ብሎም ለጤና ሥራ መረጃ ወሳኝና ህይወት እንደመሆኑ ግብዓቶቹ ይህንን ችግር ከመፍታት አንፃር አይነተኛ ሚና እንደሚኖራቸው ተናግረዋል።
ከጤና ሚኒስቴር የተገኙትን 18 አምቡላንሶች፣ 20 ሞተር ሳይክሎችና 285 ኮምፒውተሮች ለሁሉም ዞኖች በፍትሐዊነት ድጋፍ የተደረገ መሆኑን ገልፀው ድጋፍ ያደረጉ አካላትን አመስግነዋል።
የተደረጉ ድጋፎች ለታለመላቸው አላማ እንዲውሉም አሳስበዋል።
የደቡብ ኦሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ታምራት አሰፋ፣ የጋርዱላ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ካኛልቤ እና የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ይሁን ጋሎ በጋር በሰጡት አሰተያየት፤ በድጋፉ መደሰታቸውን ገልጸው የጤና ልማት ሥራዎችን በተለይም ለእናቶችና ህፃናት ብሎም ለድንገተኛ አደጋዎች አገልግሎት ተደራሽነታችንን እንድናሰፋ የሚያስችለን ነው ብለዋል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ