ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ የዜጎች ኑሮን ለማሻሻል በየአካባቢው ያሉ የተፈጥሮ ሀብቶችን በአግባቡ በመጠቀም በግብርናው ዘርፍ ዘላቂ ለውጥ ማምጣት ይጠበቅብናል ብለዋል።
በዚህ ሂደት በዘርፉ ሥራውን በቀጥታ የሚመሩ የግብርና ባለሙያዎች አርሶና አርብቶ አደር ማህብረሰቡ የአመራረትና የአረባብ ዘዴያቸውን በአዳዲስ አሠራሮች በመቀየር ሁሉ አቀፍ ለውጥ ለማስመዝገብ ተግተው መሥራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ በአቶ ኃ/ማርያም ተስፋዬ ስልጠናው በሀገር ደረጃ በግብርናው ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን በእጥፍ በማሳደግ የግብርናውን ክፍለ ኢኮኖሚውን ፈጣን ሽግግር ለማድረግ ታስቦ እንደሆነ ተናግረዋል ።ዘርፉን ማዘመንና አዳዲስ አሠራሮችን ተግባራዊ ማድረግ ቁልፍ ተግባር ተደርጎ እየተሠራ እንዳለም ተብራርቷል ።
በ2023 ዓ/ም ከክልል አልፎ እንደ አገር ዘመናዊ ተክኖሎጂ መጠቀም ፣ህብረተሰቡን ከድህነት ማለቀቅ፣ በሀገሪቱ ለውጥና ብልጽግና ጉዞ ላይ በግብርናው ዘርፍ ሽግግር ማድረግ ግብ ተይዞ እየተሠራ እንዳለም ተገልጿል ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የእንስሳት ጤናና ግብዓት አቅርቦት ኃላፊ ዶ/ር አዲሱ ኢዮብ ዜጎች ከተረጅነት ወደ ምርታማነት እንዲሸጋገሩ ፣የግብርና ባለሙያዎች እኩል የሥራ አቅም እንዲኖራቸውና በአጠቃላይ በግብርናው ዘርፍ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ታስቦ ስልጠናው መዘጋጀቱን አብራተዋል።
ዘጋቢ : ተመስገን አበራ-ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ