በዲላ ከተማ የጥምቀት በዓል በሃይማኖታዊ ሥነ ስርዓት እየተከበረ ነው
ሀዋሳ፡ ጥር 11/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በዲላ ከተማ የጥምቀት በዓል በሃይማኖታዊ ሥነ ስርዓት እየተከበረ ነው፡፡
ይህንን የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የጥምቀት በዓል ስናከብር ከክርስቶስ የተማርነውን ትህትና በመተግበር ሊሆን እንደሚገባ የጌዴኦ ኮሬ ቡርጂ ሃገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብፁዕ አቡነ ገሪማ ተናግረዋል።
አክለውም በጥምቀቱ ባገኘነው በረከት መነሻ ልጆቻችንን ከአልባለ ቦታ እንዳይውሉ በማስተማር በኃይማኖት አንጸን ልናሳድጋቸው ይገባል ሲሉ ለህዝበ ክርስቲያኑ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
አሁን ላይ የጥምቀት ስርዓቱ ከተከናወነ በኃላ ባታ ለማሪያም፣ ልደታ ለማሪያም፣ ኢየሱስ እና ሌሎች ታቦታት በታላቅ ኃይማኖታዊ ሥርዓት ወደ መንበራቸው እየተመለሱ ሲሆን ቀሪዎቹ ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት እንደሚመለሱ ተገልጿል።
ዘጋቢ: እንግዳየሁ ቆሳ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ