በዲላ ከተማ የጥምቀት በዓል በሃይማኖታዊ ሥነ ስርዓት እየተከበረ ነው
ሀዋሳ፡ ጥር 11/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በዲላ ከተማ የጥምቀት በዓል በሃይማኖታዊ ሥነ ስርዓት እየተከበረ ነው፡፡
ይህንን የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የጥምቀት በዓል ስናከብር ከክርስቶስ የተማርነውን ትህትና በመተግበር ሊሆን እንደሚገባ የጌዴኦ ኮሬ ቡርጂ ሃገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብፁዕ አቡነ ገሪማ ተናግረዋል።
አክለውም በጥምቀቱ ባገኘነው በረከት መነሻ ልጆቻችንን ከአልባለ ቦታ እንዳይውሉ በማስተማር በኃይማኖት አንጸን ልናሳድጋቸው ይገባል ሲሉ ለህዝበ ክርስቲያኑ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
አሁን ላይ የጥምቀት ስርዓቱ ከተከናወነ በኃላ ባታ ለማሪያም፣ ልደታ ለማሪያም፣ ኢየሱስ እና ሌሎች ታቦታት በታላቅ ኃይማኖታዊ ሥርዓት ወደ መንበራቸው እየተመለሱ ሲሆን ቀሪዎቹ ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት እንደሚመለሱ ተገልጿል።
ዘጋቢ: እንግዳየሁ ቆሳ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
በተቋማትና በባለሙያዎች መካከል የውድድር መንፈስ በመፍጠር ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የቀቤና ልዩ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጌዴኦ ዞን በ2017 ዓ.ም በመኸር እርሻ ከ24 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ለመሸፈን አቅዶ እየሠራ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ
”የምንተክላቸው ችግኞች ለትውልድ ተሻጋሪ ትሩፋትን የሚያስገኙ ናቸው” – ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ