በዲላ ከተማ የጥምቀት በዓል በሃይማኖታዊ ሥነ ስርዓት እየተከበረ ነው
ሀዋሳ፡ ጥር 11/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በዲላ ከተማ የጥምቀት በዓል በሃይማኖታዊ ሥነ ስርዓት እየተከበረ ነው፡፡
ይህንን የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የጥምቀት በዓል ስናከብር ከክርስቶስ የተማርነውን ትህትና በመተግበር ሊሆን እንደሚገባ የጌዴኦ ኮሬ ቡርጂ ሃገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብፁዕ አቡነ ገሪማ ተናግረዋል።
አክለውም በጥምቀቱ ባገኘነው በረከት መነሻ ልጆቻችንን ከአልባለ ቦታ እንዳይውሉ በማስተማር በኃይማኖት አንጸን ልናሳድጋቸው ይገባል ሲሉ ለህዝበ ክርስቲያኑ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
አሁን ላይ የጥምቀት ስርዓቱ ከተከናወነ በኃላ ባታ ለማሪያም፣ ልደታ ለማሪያም፣ ኢየሱስ እና ሌሎች ታቦታት በታላቅ ኃይማኖታዊ ሥርዓት ወደ መንበራቸው እየተመለሱ ሲሆን ቀሪዎቹ ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት እንደሚመለሱ ተገልጿል።
ዘጋቢ: እንግዳየሁ ቆሳ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ከ23 ሚሊየን በላይ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እንደሚተከሉ ተገለጸ
በግንቦት እና ሰኔ 2018 ዓ.ም ወራት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ፣ በቱሪዝም፣ በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በዲጂታል ኢትዮጵያ፣ በሀገር በቀል ሪፎርም እና ቀጣናዊ ዲፕሎማሲ ዙሪያ ላይ ያተኮሩ የተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ክንውኖችን አድርገዋል።
በህገወጥ መንገድ ከሀገር መውጣት ከህግ፣ ከደህንነት እና ከማህበራዊ አንፃር ከባድ ችግሮችን እንደሚያስከትል ተገለጸ