በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት በሆሳዕና ከተማ የጥምቀት ስርዓት እየተከናወነ ይገኛል
በዓሉ ኢየሱስ ክርስቶስ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ በመሄድ ፈጣሪ ሆኖ ሳለ በፍጡሩ ዮሐንስ እጅ በመጠመቅ ለሰው ልጆች ታላቅ ትህትናውን ያስተማረበት ታላቅ በዓል መሆኑን አባቶች በአስተምህሮታቸው ወቅት ገልፀዋል።
መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ኢየሱስ ክርስቶስን ባንተ መጠመቅ ሲገባኝ አንተን ላጠምቅ አይገባኝም ሲል ክርስቶስም “ጽድቅን ሁሉ መፈፀም ይገባናል” በማለት በሰው እጅ ሲጠመቅ ለሰው ልጆች ድህነት አርዓያ መሆኑን ያመላክታል ሲሉም ገልፀዋል።
የጥምቀት በዓል ክርስቶስ በልደቱ ሰማይን ምድርን እንዳስታረቀ ሁሉ በዛሬው የጥምቀት እለት ደግሞ በጥንተ ጠላት ዲያብሎስ በዮርዳኖስ ወንዝ የተቀበረን የእዳ ደብዳቤ በመቅደድ የሰው ልጆች ፍፁም ነፃነትን እንዲቀዳጅ ያደረገበት ቀን መሆኑን ጠቁመው በዓሉን መልካም ተግባራትን ሁሉ በመከወን ከአምላካችን በረከት የምናገኝበት ሊሆን ይገባል ሲሉም በትምህርታቸው አስገንዝበዋል።
ዘጋቢ: አማኑኤል አጤቦ – ከሆሳዕና ጣቢያችን
More Stories
በተቋማትና በባለሙያዎች መካከል የውድድር መንፈስ በመፍጠር ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የቀቤና ልዩ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጌዴኦ ዞን በ2017 ዓ.ም በመኸር እርሻ ከ24 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ለመሸፈን አቅዶ እየሠራ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ
”የምንተክላቸው ችግኞች ለትውልድ ተሻጋሪ ትሩፋትን የሚያስገኙ ናቸው” – ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ