በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት በሆሳዕና ከተማ የጥምቀት ስርዓት እየተከናወነ ይገኛል
በዓሉ ኢየሱስ ክርስቶስ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ በመሄድ ፈጣሪ ሆኖ ሳለ በፍጡሩ ዮሐንስ እጅ በመጠመቅ ለሰው ልጆች ታላቅ ትህትናውን ያስተማረበት ታላቅ በዓል መሆኑን አባቶች በአስተምህሮታቸው ወቅት ገልፀዋል።
መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ኢየሱስ ክርስቶስን ባንተ መጠመቅ ሲገባኝ አንተን ላጠምቅ አይገባኝም ሲል ክርስቶስም “ጽድቅን ሁሉ መፈፀም ይገባናል” በማለት በሰው እጅ ሲጠመቅ ለሰው ልጆች ድህነት አርዓያ መሆኑን ያመላክታል ሲሉም ገልፀዋል።
የጥምቀት በዓል ክርስቶስ በልደቱ ሰማይን ምድርን እንዳስታረቀ ሁሉ በዛሬው የጥምቀት እለት ደግሞ በጥንተ ጠላት ዲያብሎስ በዮርዳኖስ ወንዝ የተቀበረን የእዳ ደብዳቤ በመቅደድ የሰው ልጆች ፍፁም ነፃነትን እንዲቀዳጅ ያደረገበት ቀን መሆኑን ጠቁመው በዓሉን መልካም ተግባራትን ሁሉ በመከወን ከአምላካችን በረከት የምናገኝበት ሊሆን ይገባል ሲሉም በትምህርታቸው አስገንዝበዋል።
ዘጋቢ: አማኑኤል አጤቦ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ