በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት በሆሳዕና ከተማ የጥምቀት ስርዓት እየተከናወነ ይገኛል
በዓሉ ኢየሱስ ክርስቶስ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ በመሄድ ፈጣሪ ሆኖ ሳለ በፍጡሩ ዮሐንስ እጅ በመጠመቅ ለሰው ልጆች ታላቅ ትህትናውን ያስተማረበት ታላቅ በዓል መሆኑን አባቶች በአስተምህሮታቸው ወቅት ገልፀዋል።
መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ኢየሱስ ክርስቶስን ባንተ መጠመቅ ሲገባኝ አንተን ላጠምቅ አይገባኝም ሲል ክርስቶስም “ጽድቅን ሁሉ መፈፀም ይገባናል” በማለት በሰው እጅ ሲጠመቅ ለሰው ልጆች ድህነት አርዓያ መሆኑን ያመላክታል ሲሉም ገልፀዋል።
የጥምቀት በዓል ክርስቶስ በልደቱ ሰማይን ምድርን እንዳስታረቀ ሁሉ በዛሬው የጥምቀት እለት ደግሞ በጥንተ ጠላት ዲያብሎስ በዮርዳኖስ ወንዝ የተቀበረን የእዳ ደብዳቤ በመቅደድ የሰው ልጆች ፍፁም ነፃነትን እንዲቀዳጅ ያደረገበት ቀን መሆኑን ጠቁመው በዓሉን መልካም ተግባራትን ሁሉ በመከወን ከአምላካችን በረከት የምናገኝበት ሊሆን ይገባል ሲሉም በትምህርታቸው አስገንዝበዋል።
ዘጋቢ: አማኑኤል አጤቦ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ