የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አብርሃም ቲርካሶ እንዳሉት፤ በክልሉ የከተራና የጥምቀት በዓላት በሰላማዊ ሁኔታ ተከብሮ እንዲጠናቀቅ በክልሉ በሚገኙ ሁሉም አካባቢዎች የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተደርገዋል።
በክልሉ ጥር 10 ማለትም በከተራ በዓል 9 መቶ 24 ታቦታት ከመንበረ ክብራቸዉ ተነስተው ወደ ተዘጋጀላቸው ማረፊያ ስፍራ እንደሚንቀሳቀሱ ምክትል ኮሚሽነር አብርሃም ጠቅሰው፤ ታቦታቱ በሚያልፉባቸው መንገዶች ሁሉ እንቅስቃሴዎችን የሚያስተጓጉሉ ነገሮች እንዳይኖሩ ከሀይማኖት አባቶች፣ ከወጣቶችና ከማህበረሰቡ ጋር ሰፊ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
በክልሉ የከተራና የጥምቀት በዓላት ለተከታታይ 4 ቀናት በተለያዩ ሀይማኖታዊ ክዋኔዎች የሚከበሩ መሆናቸውን ጠቅሰዉ፤ በዓሉን ለማክበር ከሀገር ወስጥም ሆነ ከዉጭ የሚመጡ እንግዶች በሰላም እንዲመለሱ ለማድረግ ህብረተሰቡን ያሳተፈ አስተማማኝ የፀጥታ ስራ እየተሰራ ነዉ ብለዋል፡፡
የከተራና የጥምቀት በዓላት ላይ የስርቆትና ሌሎች ወንጀሎችም ሊከሰቱ ስለሚችሉ ምዕመኑ አስፈላጊዉን ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበትም አሳበዋል፡፡
ህብረተሰቡ በዓሉን ለማክበር በሚያደረገው በማንኛውም እንቅስቃሴ ራሱን ከአደጋ በመጠበቅ ሊሆን እንደሚገባም ተናግረዋል።
ምዕመኑ በዓሉን በሚያከብርበት ወቅት ያልተገባ ድርጊት የሚፈጽሙትን ለፀጥታ አካላት ጥቆማ በመስጠት ትብብሩን እንዲያሳይም ጠይቀዋል።
ምክትል ኮሚሽነር አብርሃም በመጨረሻም ለመላው የእምነቱ ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ዘጋቢ: ተሻለ ከበደ – ከሆሳዕና ጣቢያችን
More Stories
ስፖርት በአንድ አካባቢ የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ከማቀራረቡም በተጨማሪም ለአንድ አካባቢ ሰላም መስፈን ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት የጉራጌ ዞን አስተዳደር ገለጸ
አምረፍ ሄልዝ አፍሪካ ግብረ ሰናይ ድርጅት ለበርካታ ዓመታት የጤናውን ዘርፍ በመደገፍ የማይተካ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ
ከእርሻ መሬት መጠቀሚያ ግብር 20 ሚሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ዞን የጎምቦራ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ ቤት አስታወቀ