የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አብርሃም ቲርካሶ እንዳሉት፤ በክልሉ የከተራና የጥምቀት በዓላት በሰላማዊ ሁኔታ ተከብሮ እንዲጠናቀቅ በክልሉ በሚገኙ ሁሉም አካባቢዎች የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተደርገዋል።
በክልሉ ጥር 10 ማለትም በከተራ በዓል 9 መቶ 24 ታቦታት ከመንበረ ክብራቸዉ ተነስተው ወደ ተዘጋጀላቸው ማረፊያ ስፍራ እንደሚንቀሳቀሱ ምክትል ኮሚሽነር አብርሃም ጠቅሰው፤ ታቦታቱ በሚያልፉባቸው መንገዶች ሁሉ እንቅስቃሴዎችን የሚያስተጓጉሉ ነገሮች እንዳይኖሩ ከሀይማኖት አባቶች፣ ከወጣቶችና ከማህበረሰቡ ጋር ሰፊ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
በክልሉ የከተራና የጥምቀት በዓላት ለተከታታይ 4 ቀናት በተለያዩ ሀይማኖታዊ ክዋኔዎች የሚከበሩ መሆናቸውን ጠቅሰዉ፤ በዓሉን ለማክበር ከሀገር ወስጥም ሆነ ከዉጭ የሚመጡ እንግዶች በሰላም እንዲመለሱ ለማድረግ ህብረተሰቡን ያሳተፈ አስተማማኝ የፀጥታ ስራ እየተሰራ ነዉ ብለዋል፡፡
የከተራና የጥምቀት በዓላት ላይ የስርቆትና ሌሎች ወንጀሎችም ሊከሰቱ ስለሚችሉ ምዕመኑ አስፈላጊዉን ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበትም አሳበዋል፡፡
ህብረተሰቡ በዓሉን ለማክበር በሚያደረገው በማንኛውም እንቅስቃሴ ራሱን ከአደጋ በመጠበቅ ሊሆን እንደሚገባም ተናግረዋል።
ምዕመኑ በዓሉን በሚያከብርበት ወቅት ያልተገባ ድርጊት የሚፈጽሙትን ለፀጥታ አካላት ጥቆማ በመስጠት ትብብሩን እንዲያሳይም ጠይቀዋል።
ምክትል ኮሚሽነር አብርሃም በመጨረሻም ለመላው የእምነቱ ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ዘጋቢ: ተሻለ ከበደ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
ሀገራዊ ምክክር፤ የመደማመጥ፣ የመግባባትና የጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት ነው!
ከ23 ሚሊየን በላይ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እንደሚተከሉ ተገለጸ
በግንቦት እና ሰኔ 2018 ዓ.ም ወራት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ፣ በቱሪዝም፣ በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በዲጂታል ኢትዮጵያ፣ በሀገር በቀል ሪፎርም እና ቀጣናዊ ዲፕሎማሲ ዙሪያ ላይ ያተኮሩ የተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ክንውኖችን አድርገዋል።