ሀዋሳ፡ ጥር 09/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዲላ ክላስተር የውኃ፣ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት የብልጽግና ፓርቲ መሠረታዊ የድርጅት አባላት ኮንፍራንስ እየተካሄደ ይገኛል።
ኮንፈረንሱ 2ኛው የብልጽግና ፓርቲ ጉባኤ ቅድመ ጉባኤ አካል መሆኑን በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የዲላ ክላስተር አስተባባሪ እና የውኃ ማዕድን እና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ እንዲሁም የመሰረታዊ ድርጅት አባል ኢንጅነር አክልሉ አዳኝ ተናግረዋል።
አክለውም በቀረበው ሰነድ በግልጽ የተቀመጡ አቅጣጫዎች መነሻ፤ በመጣንበት መንገድ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ እና በዲፕሎማሲ ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤቶች መኖራቸውን ጠቁመው፤ ውጤቶቹ የጋራ በመሆናቸው ማስፋት እንደሚገባ አሳስበዋል።
በመድረኩ የማዕከላዊ ኮሚቴ ሪፖርት፣ የህገ ደንብ ማሻሻያ፣ የመሰረታዊ ድርጅት የ6 ወር አፈጻጸም ሪፖርት እና ቀጣይ አቅጣጫ ማስቀመጥ፣ የኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ሪፖርት እና የጉባኤ ተሳታፊዎች ምርጫ እንደሚከናወን በመርሃ ግብሩ ተመላክቷል።
በኮንፈረንሱ የክላስተሩ አመራሮችና የብልጽግና ፓርቲ መሠረታዊ ድርጅት አባላት እንዲሁም የመሰረታዊ ድርጅት ኢንስፔክሽንና ሥነ ምግባር ኮሚሽን አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል።
ዘጋቢ: እንግዳየሁ ቆሳ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ