ሀዋሳ፡ ጥር 07/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሆሳዕና እና አከባቢ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሶሎ መዘምራን ሕብረት ከሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ለተወጣጡ አቅመ ደካሞች ከ276 ሺህ ብር በላይ ዋጋ ያለውን ዱቄትና ዘይት ድጋፍ አደረጉ።
የበጎ አገልግሎት ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም የሀዲያ ዞን አስተዳደር ገልጿል።
የሆሳዕና እና አካባቢው ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሶሎ መዘምራን ሕብረት አስተባባሪ ዘማሪ ዮሴፍ ሳሙኤል ሕብረቱ ከመንፈሳዊ አገልግሎት ባሸገር ከዚህ ቀደም በተለያዩ በጎ ተግባር አገልግሎቶች ላይ በመሳተፍ እየሰራ መቆየቱን አስታውሰዋል።
በዕለቱ ከሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ለተወጣጡ ለ100 አቅም ደካሞች ከ276 ሺህ ብር በላይ ወጪ በማድረግ ለእያንዳንዳቸው 25 ኪሎ ግራም የስንዴ ዱቄትና 3 ሊተር ዘይት ድጋፍ ማድረጋቸውን ተናግረዋል ።
ወጪው ሙሉ በሙሉ ደቡብ አፍርካ ከሚገኘው ቪራይት ኤፍ ቢ አይ ቤተክርስቲያን የተገኘ መሆኑንም ጠቁመዋል ።
ከዚህ በተጨማሪም በከተማው የጽዳት ዘመቻ ስራን መስራታቸውን ገልጸዋል ።
የአሁኑ ድጋፍ ለሁለተኛ ዙር መሆኑን የተናገሩት ዘማሪ ዮሴፍ፥ በቀጣይም ይኸው ድጋፍ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል ።
የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዳዊት ጡምደዶ በበኩላቸው መንግስት ከጀመረው ሰዉ ተኮር ተግባር አቅመ ደካሞችን መርዳት አንዱ መሆኑን ተናግረዋል ።
ከንቲባው አክለውም ድጋፍ ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበው ሁሌም ተረጂ ሆኖ መኖር ሳይሆን የተሰጠንን ዕድል በመጠቀም ሠርቶ ለመለወጥ መትጋት እንዳሚገባ አሳስበዋል ።
በድጋፍ ስነስርዓቱ ላይ የተገኙ የሀዲያ ዞንዋና አስተዳዳሪ ተወካይ አቶ ታምራት አኑሎ የተቸገሩትን መርዳት በሁሉም ዘንድ ዋጋ ያለው በጎ ተግባር መሆኑን ጠቁመዋል ።
ይህ በጎ ድጋፍ ሰብአዊና ሐይማኖታዊ ኃላፊነት በመሆኑ በሁሉም ዘንድ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አሳስበዋል።
ድጋፍ የተደረገላቸው ወገኖችም በተደረገላቸው ድጋፍ መደሰታቸውን ገልጸዋል።
ዘጋቢ: ታምራት አለሙ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ