የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የጌዴኦ አግሮፎረስትሪ ተጠብቆ እንዲቆይ የድርሻዋን እየተወጣች ነው ሲል የጌዴኦ ዞን አስተዳደር ገልጿል።
ዙሪያዋን በሀገር በቀል ዛፎች የተከበበችው የሀንዲዳ መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን ከዲላ ከተማ በ7 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ትገኛለች።
የቤተክርስቲያኗ አስተዳዳሪ መላከሰላም ቀሲስ ጥላሁን ተሰማ ከ40 ዓመት በፊት 4 ሺህ የዛፍ ችግኞችን በማምጣት መትከላቸውን ተናግረዋል።
ቤተክርስቲያኗ ያላት ቅርስም ሆነ ትልቁ ውበቷ ደን ነው ያሉት አቶ መኮንን ሰይፉ፤ ለአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ከማበጀት ባለፈ የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ እየተሰራ እንዳለ ጠቁመዋል።
ትውልድን በስነ-ምግባር ለማነጽ ከዚህ ቀደም ሰሜን ላይ ብቻ የነበረው የአብነት ትምህርት ቤት ለመገንባት ከ60 ሚሊየን ብር በላይ በሀገረ ስብከቱ ተመድቦ እንቅስቃሴ መጀመሩም ተገልጿል።
የሀንዲዳ ደብረሰላም መድሐኒዓለም ቤተክርስቲያን በአካባቢ ጥበቃና የተፈጥሮ ሀብት አያያዝ የበኩሏን እየተወጣች ነው ያሉት የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶክተር ዝናቡ ወልዴ፤ በUNESCO ለተመዘገበው አግሮፎረስትሪ በቤተክርስቲያኗ የሚገኙ የረዥም ዘመን ጥብቅ ደኖች ትልቅ አበርክቶ እንዳላቸው ተናግረዋል።
ቤተክርስቲያኗ ከተፈጥሮ ጥበቃ ባለፈ በትምህርቱ ዘርፍ እየሰራች ያለችውን ስራ ዶ/ር ዝናቡ አድንቀዋል።
ዘጋቢ፡ ውብሸት ካሣሁን – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
የሚዛን አማን ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት በበጀት አመቱ ከማህበረሰቡ በመቀናጀት የከተማዋን ሠላምና ፀጥታ ለማስከበር ከፍተኛ ስራ መስራቱን ገለጸ
ጽዱ ከተማ ለመፍጠር የህብረተሰብ ተሳትፎ ማጠናከር እንደሚገባ የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
ፖሊስ ከመደበኛ ስራዉ ጎን ለጎን ከማህበረሰቡ ጋር በጋራ የሚያካሂደዉን የልማት ስራ አጠናክሮ ማስቀጠል እንዳለበት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ