በብሔሩ ዘንድ በጥር ወር የሚከበረው የ2017 ዓ.ም የዘመን መለወጫ ዳራሮ በዓል የጌዴኦ ህዝብ የባህል አስተዳዳሪ መሪ አባ ጋዳ ቢፎሚ ዋቆ ቤት ተከብሯል፡፡
ዛሬ በብሄሩ ዘንድ ጥር 1 የአዲስ ዓመት መግቢያ በዓል በመሆን ነው የተከበረው።
የ2017 ዓ.ም የዘመን መለወጫ ዳራሮ በዓል በዲላ ዙሪያ ወረዳ ወቸማ ሆጢቻ በሚገኘው ፋዬሞ ሶንጎ በሁሉቃ፣ በፋጎና በተለያዩ ኩነቶች መከበር ጀምሯል።
ዳራሮ የጌዴኦ ህዝብ የአዲስ ዓመት ማብሰሪያና የአዲስ ዓመት ተስፋ መሰነቂያ የዕርቅና የይቅርታ በዓል ነው።
በዓሉ የሚከበረው ከአሮጌው ዓመት ወደ አዲስ ዓመት ያሸጋገረው ፈጣሪ የሚመሰገንበት ከጥንት አባቶቻችን የመጣውን አኩሪ ባህል ለቀጣይ ትውልድ በማስተማር ለማሸጋገር ዓላማ ያደረገ ነው።
በብሔሩ ዘንድ በጥር ወር የሚከበረው የ2017 ዓ.ም የዘመን መለወጫ ዳራሮ በዓል የጌዴኦ ህዝብ የባህል አስተዳዳሪ መሪ አባ ጋዳ ቢፎሚ ዋቆ ቤት ተከብሯል፡፡
የዘንድሮው ዳራሮ በዓል በአባ ጋዳ፣ በአባ ሮጋዎች፣ በሁላቲ ሃይቻዎች እና በዎዮዎች ቤት በየደረጃ እየተከበረ ይገኛል።
በበዓሉ በሀገሪቱ ያሉ የተለያዩ ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች እንዲጠፉ ጸሎትና ልመና ተደርጓል።
ይህንን ለፈጣሪ ልመናና ምስጋና የሚቀርብበት በዓል ለትውልድ ለማሸጋገር እና ጠብቆ ለማቆየት እየተሰራ እንዳለም ተገልጿል።
ዳራሮ በዓል በየዓመቱ በጥር ወር ውስጥ ከአንጋፋው ኦዳ ያአ ሶንጎ መከበር የሚጀመር ሲሆን በሁሉም ወረዳዎች በሚገኙት አንጋፋ ሶንጎች እየተከበረ ቆይቶ ማጠቃለያ በዞን ደረጃ በዲላ ስታዲየም በድምቀት በተለያዩ ዝግጅቶች ይከበራል።
የዘንድሮው ዳራሮ በዓል በቡሌ ወረዳ በሚገኘው አንጋፋው ኦዳ ያአ ሶንጎ ጥር 03/2017 ዓ.ም መከበር እንደሚጀመር ተገልጿል።
ዘጋቢ፡ ውብሸት ካሣሁን – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
ማረሚያ ቤቶች ከማረምና ማነፅ ሥራዎች በተጨማሪ የልማት ሥራዎችን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ የፌደራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ገለፀ
የሀገራችንን ሠላምና ልማት ለማስቀጠል የበጎ ፈቃድ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ገለፀ
ተመራቂ ተማሪዎች በሰለጠኑበት የሙያ መስክ ያላቸዉን እዉቀትና ክህሎት ተጠቅመዉ ዘመኑን የሚመጥን ስራ በመስራትና ተወዳዳሪ በመሆን ሀገራዊ ሀላፊነታቸዉን መወጣት እንዳለባቸዉ ተገለፀ