የወልቂጤ ከተማ የወንጌላዊያን አብያተ ክርስቲያናት ወጣቶች ህብረት ከወልቂጤ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር የገናን በዓልን ምክንያት በማድረግ ለአቅመ ደካማ የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ አደረገ
የወልቂጤ ከተማ ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድር የገና በዓል ፍቅር እና፣ አንድነት ጎልቶ የሚታይበት በመሆኑ ይህንን በዓል ተሳቢ በማድረግ በከተማ አስተዳደር አጋር ድርጅቶች ከሃይማኖት ተቋማት ጋር እየተደረገ ያለው ድጋፍ ይበል የሚያሰኝ ተግባር በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንደለበት ተናግረዋል።
በጎ በማድረግ የሚገኝውን የህልና እርከታና ደስታ በምንም የማይገኝ እንደሆነ ያስታወሱት አቶ ሙራድ በዚህ መልካም ተግባር ላይ የተሳተፉ አካላትን አመስግነዋል።
የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር. ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አስራት ታደለ በበኩላቸው በከተማ ደረጃ የክረምት በጎ ፈቃድ ላይ በርካታ ወጣቶች በመሳተፍ ድጋፍ ለሚሹ አቅመ ደካሞችን በመርዳት የበኩላቸውን ሚና እየተወጡ ይገኛሉ ብለዋል ።
በወልቂጤ ከተማ አስተዳደር የሙሉ ወንጌል ቁጥር አንድ ቤተክርስቲያን አባል አቶ ቦጋላ ሃይሌ በበኩላቸው የከተማ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት የወጣቶች ዘርፍ ባለፉት በርካታ አመታት ከከተማ አስተዳደሩ ጎን በመቆም በማህበራዊ እና በኢኮኖሚያዊ ዘርፍ ላይ በርካታ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ተናግረዋል ።
በተለይም ወጣቶች ማዕድ ማጋራት ፕሮግራሞችን በማዘጋጀት፣ በማረሚያ ተቋም ያሉ ታራሚዎች ካላቸው በማካፈል እና በሌሎችም ተግባራት ላይ በመሳተፍ የድርሻውን እየተወጡ መሆናቸውን አስረድተዋል ።
ድጋፍ የተደረገላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች በሰጡት አስታያየት ድጋፉ እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል።
ዘጋቢ ፡ ደጋጋ ሂሳቦ-ከወልቂ-ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ