የሶያማ ከተማ አስተዳደር የከተማ ግብርና ዩኒት በበኩሉ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ችግሩን ለመቅረፍ እንደሚሠራ አስታውቋል።
የሶያማ ከተማ 01 እና 02 ቀበሌ ነዋሪ አቶ መሐመድ ጨርቆስ እና አቶ አሊ ሮጌ፤ በግማሽ ሄክታር መሬት ላይ ጥቅል ጎመን፣ ቲማቲም እና ሌሎች አትክልቶችን እያለሙ ቢሆንም የመስኖ ውሃ በበቂ ሁኔታ ወደአካባቢው አለመድረስና የዋግ በሽታ ፈተና እንደሆነባቸው ጠቁመው የሚመለከተው አካል ችግሩን እንዲፈታም ጠይቀዋል።
አቶ ሶካ ማሬ በበኩላቸው በአካባቢው ሽንኩርትና ጥቅል ጎመን እያለሙ ከዚህ በፊት ከለማው 2 መቶ ሺህ ብር እንዳገኙና የአሁኑም ጥሩ ደረጃ ላይ ያለ ቢሆንም የመስኖ ውሃ ቦይ ሳይጠናቀቅ በመቅረቱ የተፈለገውን ያህል ውሃ ስለማይደረስ መቸገራቸውን ተናግረዋል።
በቡርጂ ዞን ሶያማ ከተማ አስተዳደር የከተማ ግብርና ዩኒት መሪ አቶ መልጄ ሞሌ በበኩላቸው፤ እየተነሱ ያሉ ቅሬታዎች ተገቢ መሆናቸውንና በዩኒቱ አቅም ብቻ የሚፈታ ባለመሆኑ ከከተማ አስተዳደሩ እና በዞኑ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ችግሩን ለመፍታት እንደሚሠሩ ገልጸዋል።
ዘጋቢ፡ ቦጋለ ሉሳ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ