የሶያማ ከተማ አስተዳደር የከተማ ግብርና ዩኒት በበኩሉ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ችግሩን ለመቅረፍ እንደሚሠራ አስታውቋል።
የሶያማ ከተማ 01 እና 02 ቀበሌ ነዋሪ አቶ መሐመድ ጨርቆስ እና አቶ አሊ ሮጌ፤ በግማሽ ሄክታር መሬት ላይ ጥቅል ጎመን፣ ቲማቲም እና ሌሎች አትክልቶችን እያለሙ ቢሆንም የመስኖ ውሃ በበቂ ሁኔታ ወደአካባቢው አለመድረስና የዋግ በሽታ ፈተና እንደሆነባቸው ጠቁመው የሚመለከተው አካል ችግሩን እንዲፈታም ጠይቀዋል።
አቶ ሶካ ማሬ በበኩላቸው በአካባቢው ሽንኩርትና ጥቅል ጎመን እያለሙ ከዚህ በፊት ከለማው 2 መቶ ሺህ ብር እንዳገኙና የአሁኑም ጥሩ ደረጃ ላይ ያለ ቢሆንም የመስኖ ውሃ ቦይ ሳይጠናቀቅ በመቅረቱ የተፈለገውን ያህል ውሃ ስለማይደረስ መቸገራቸውን ተናግረዋል።
በቡርጂ ዞን ሶያማ ከተማ አስተዳደር የከተማ ግብርና ዩኒት መሪ አቶ መልጄ ሞሌ በበኩላቸው፤ እየተነሱ ያሉ ቅሬታዎች ተገቢ መሆናቸውንና በዩኒቱ አቅም ብቻ የሚፈታ ባለመሆኑ ከከተማ አስተዳደሩ እና በዞኑ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ችግሩን ለመፍታት እንደሚሠሩ ገልጸዋል።
ዘጋቢ፡ ቦጋለ ሉሳ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ሀገራዊ ምክክር፤ የመደማመጥ፣ የመግባባትና የጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት ነው!
ከ23 ሚሊየን በላይ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እንደሚተከሉ ተገለጸ
በግንቦት እና ሰኔ 2018 ዓ.ም ወራት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ፣ በቱሪዝም፣ በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በዲጂታል ኢትዮጵያ፣ በሀገር በቀል ሪፎርም እና ቀጣናዊ ዲፕሎማሲ ዙሪያ ላይ ያተኮሩ የተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ክንውኖችን አድርገዋል።