የሶያማ ከተማ አስተዳደር የከተማ ግብርና ዩኒት በበኩሉ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ችግሩን ለመቅረፍ እንደሚሠራ አስታውቋል።
የሶያማ ከተማ 01 እና 02 ቀበሌ ነዋሪ አቶ መሐመድ ጨርቆስ እና አቶ አሊ ሮጌ፤ በግማሽ ሄክታር መሬት ላይ ጥቅል ጎመን፣ ቲማቲም እና ሌሎች አትክልቶችን እያለሙ ቢሆንም የመስኖ ውሃ በበቂ ሁኔታ ወደአካባቢው አለመድረስና የዋግ በሽታ ፈተና እንደሆነባቸው ጠቁመው የሚመለከተው አካል ችግሩን እንዲፈታም ጠይቀዋል።
አቶ ሶካ ማሬ በበኩላቸው በአካባቢው ሽንኩርትና ጥቅል ጎመን እያለሙ ከዚህ በፊት ከለማው 2 መቶ ሺህ ብር እንዳገኙና የአሁኑም ጥሩ ደረጃ ላይ ያለ ቢሆንም የመስኖ ውሃ ቦይ ሳይጠናቀቅ በመቅረቱ የተፈለገውን ያህል ውሃ ስለማይደረስ መቸገራቸውን ተናግረዋል።
በቡርጂ ዞን ሶያማ ከተማ አስተዳደር የከተማ ግብርና ዩኒት መሪ አቶ መልጄ ሞሌ በበኩላቸው፤ እየተነሱ ያሉ ቅሬታዎች ተገቢ መሆናቸውንና በዩኒቱ አቅም ብቻ የሚፈታ ባለመሆኑ ከከተማ አስተዳደሩ እና በዞኑ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ችግሩን ለመፍታት እንደሚሠሩ ገልጸዋል።
ዘጋቢ፡ ቦጋለ ሉሳ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ