ፍ/ቤቶች እና የፍትህ ተቋማት በህገ መንግሥቱ የተሰጠውን የዜጎች መብት በማክበር እና በማስከበር የላቀ አስተዋጽኦ ማበርከት ይጠበቅባቸዋል ተባለ
ይህም የተባለው በቡርጂ ዞን የፍ/ቤቶች እና ፍትህ ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል ለሶስቱም ወዋቅር አመራሮች እና ባለድርሻ አካላት በተዘጋጀ የንቅናቄ መድረክ ላይ ነው።
በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የቡርጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳኜ ህዶ ፍርድ ቤቶች እና የፍትህ ተቋማት ለተገልጋዩ ህብረ ሰብ ፈጣን ፣ ግልፅ እና ታአማንነት ያለውን አግልግሎት መስጠት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።
የቡርጂ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንት አሊ መሐመድ በበኩላቸው ፍ/ቤቶች በህገ መንግሥት የተሰጠውን የዜጎች መብት በማክበርና በማስከበር የላቀ አስተዋጽኦ ማበርከት እንደሚጠበቅባቸው ገልጸው ለዚህም እራሱን የቻለ ሪፎርም ተነድፎለት ሀገራዊ ፣ ክልላዊና ዞናዊ ሥራዎች እንደተጀመሩ ተናግረዋል።
አክለውም ሪፎርሙ ከህዝብ ክንፍና ከባለድርሻ አካላት የተሰበሰቡ ግብዓቶችን መነሻ እንዳደረገ ጠቅሰው የቀድሞ ማሻሻያ የተገመገመበት፣ የቀጣይ የራዕይ፣ ተልዕኮ እና ግብ እንዲሁም የክትትልና የግምገማ ሥርዓት የያዘ መሆኑን ገልፀዋል።
በውይይቱ ላይ ከተሳተፉት መካከል አቶ ወየሳ ወርቁ፣ አቶ አደን ማሬ እና ሌሎችም በሰጡት አስተያየት በወይይቱ ላይ ከቀረበው ሰነድ ብዙ ግብዓት እንዳገኙና እንደ ችግር የተነሱ ጉዳዮችን ለቅመው በመውሰድ ለማስተካከል የበኩላቸውን እንደሚወጡ አንስተዋል።
ዘጋቢ : ቦጋለ ሉሳ ከይርጋ ጨፌ ቅርንጫፍ ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ