ሀዋሳ፡ ታህሳስ 17/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) አባቶቻችን ያቆዩልንን የጀፎረ ባህላዊ አውራ መንገድ ጠብቆ ለትውልድ ማስተላለፍ እንደሚገባ የጉራጌ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ ገለፁ።
“ጀፎረ ባህላዊ የምህንድስና ጥበብ” በሚል መሪ ቃል የገጠር ኮሪደር ለማልማት የተዘጋጀ የንቅናቄ መድረክ በወልቂጤ ከተማ ተካሄዷል።
የኮሪደር ልማቱ አርሶ አደሩ ባህሉንና ወጉን ጠብቆ አካባቢውን ንጹህ ለኑሮ ተስማሚ በማድረግ ዘመናዊና ቀላል የአኗኗር ስልት እንዲከተል የሚያደርግ እንደሆነም ተገልጿል፡፡
በንቅናቄ መድረኩ ላይ የተገኙት የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ እንደገለፁት አባቶቻችን ያቆዩልንን የጀፎረ ባህላዊ አውራ መንገድ ጠብቆ ለትውልድ ማስተላለፍ ይገባል።
የኮሪደር ልማቱ አርሶ አደሩ ባህሉንና ወጉን ጠብቆ አካባቢውን ንጹህ፣ ጓሮውን በዶሮ፣ በአትክልትና ፍራፍሬ፣ እንዲሁም በማርና ወተት ምርት የተትረፈረፈ በማድረግ ዘመናዊና ቀላል የአኗኗር ስልት እንዲከተል የሚያደርግ እንደሆነም አቶ ላጫ ተናግረዋል፡፡
የጉራጌ ዞን ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አለማየሁ ገብረ መስቀል በበኩላቸው ጀፎረን ከተለያዩ አደጋዎች ለመጠበቅ አባቶች ያስቀመጡትን መተዳደሪ ደንብ መተግበር ይገባል ሲሉ ጠቁመዋል።
የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ሃላፊ ወይዘሮ መሰረት አመርጋ ጀፎረ ለዘመናዊው የምህንድስና ጥበብ ፈር ቀዳጅ አስደናቂ የጉራጌ ባህላዊ አውራ መንገድ ነው ብለዋል።
ጀፎረ የተለያዩ ባህላዊ፣ ሃይማኖታዊ እና የሽምግልና ስርዓት የሚከናወንበት በርካታ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ግልጋሎቶችን እየሰጠ ይገኛል ብለዋል።
የመድረኩ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት እንደ ሃገር እየተተገበረ ያለውን የገጠር ኮሪደር ልማት አርሶአደሩን በኢኮኖሚ የበለጠ ተጠቃሚ እንዲሆን የሚያስችል ነው ብለዋል።
የጀፎረ ይዘትን በጠበቀ መልኩ የገጠር ኮሪደር ልማት በተቀመጠለት ጊዜ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ አስቻለው አማረ – ከወልቂጤ ጣቢያችን
More Stories
ገቢን በተገቢው በመሰብሰብ የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች በተገቢው መመለስ እንደሚገባ ተገለጸ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በ2017 የግብር ወቅት ከደረጃ ‘ሐ’ ግብር ከፋዮች ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱ ተገለጸ
የህብረተሰቡን ጤና ለማጎልበት የዘርፉን ተግባራት በተገቢው ለማሳካት ከምንጊዜውም በተሻለ በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ