በደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ የምሁራን ምክክር ተካሄደ
ሀዋሳ፡ ታህሳስ 15/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) “ወረዳዊ አንድነት ለጋራ ህልሞቻችን ለሁለንተናዊ ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል በደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ የምሁራን ምክክር ተካሂዷል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መስኖና ቆላማ አካባቢ ምክትል ቢሮ ሃላፊ አቶ አይዴ ሎሞዶ በመድረኩ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ማህበረሰቡን በተደጋጋሚ እየደረሰበት ካለው ተፈጥሮአዊና ሰው ሰራሽ ችግሮች በመታደግ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በማሸጋገር ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ የወረዳው ምሁራን ሀሳባቸውን አደራጅተውና አንድነታቸውን አጠናክረው መስራት እንዳለባቸው ተናግረዋል።
በወረዳው ያሉ ሶስት የመስኖ ተቋማትን በመጠቀም የግብርናውን ዘርፍ ውጤታማ በማድረግ የሚቀርቡ እርዳታዎችን እና የእንስሳት ኢንሹራንስ ገንዘብ በአግባቡ ለታለመለት አላማ በማዋል አርብቶ አደሩ ተጠቃሚ እንዲሆን ለማድረግ አመራሩና ምሁራኑ በመቀናጀት መስራት ይገባቸዋል ብለዋል።
የደቡብ ኦሞ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ታደሰ ጋልጶክ በበኩላቸው፤ አመራሩና ምሁራኑ በጋራ ተቀራርበው በመወያየት የአርብቶ አደሩን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
ከውሃ ሙላት ጋር ተያይዞ በማህበረሰቡ ላይ እየደረሰ ያለውን ጫና ለመቅረፍ በቀጣይ ከፌደራል ባለድርሻ አካላት ጋር በመስራት ዘላቂ መፍትሔ እንዲበጅለት ለማድረግ መታቀዱን ተናግረዋል።
የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ሀቴ፤ ለአርብቶ አደሩ መልካም ስራ ለመስራት ከአመራሩ ጋር በጋራ በመቀናጀትና አንድነትን በማጠናከር የአርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት ሊሰራ ይገባል ብለዋል።
ዘጋቢ፡ በናወርቅ መንግስቱ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
የሲዳማ ክልላዊ መንግሥት 5ኛ አመት የምስረታ በዓል በተለያዩ ስነ ስርዓቶች እየተከበረ ነው
በክልሉ በተያዘው የበልግ ወቅት በኩታገጠም ሩዝና በቆሎ እያለሙ ያሉ አርሶአደሮች ተስፋ ሰጪ የሆነ የምርት ውጤት እንድናይ አስችሎናል አሉ።
ችግር ፈቺ የሆኑ የጥናትና የምርምር ስራዎችን ተግባራዊ በማድረግ የህብረተሰብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አመራር አካዳሚ አስታወቀ