ሀዋሳ፡ ታህሳስ 10/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ከ121 ሚሊየን 475ሺህ ብር በላይ መሰብሰብ መቻሉን የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ገልጿል።
መምሪያው ይህንን መሰብሰብ የቻለው 245ሺህ 551 አባላቱ መሆኑንም ጠቁሟል።
የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ከአርባምንጭ ጤና መድህን አገልግሎት የ2016 ሪፖርትና የ2017 በጀት እቅድ ዙሪያ ውይይት አድርጓል።
የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሰይፉ ዋናቃ በመድረኩ እንደገለጹት፤ የጤና መድህን አገልግሎት ዜጎች አስቀድመው በሚከፍሉት አነስተኛ መዋጮ ያልተገባ የጤና ወጪ ውስጥ እንዳይገቡ የሚያደርግ መሆኑን አብራርተው በዘርፉም በርካታ ለውጦች መመዝገባቸውን ጠቁመዋል።
የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ትግበራ በዞኑ በ2008 ዓ.ም በ 3 ወረዳዎች መጀመሩንና በ2011 በጀት ዓመት 77ሺህ 848 አባላትን ማፍራት መቻሉን ጠቁመው ግንዛቤን የማሳደግ ስራ በመሰራቱ በአሁኑ ወቅትም 245ሺህ 551 የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባላትን በማፍራት 121ሚሊየን 475ሺህ 106 ሺህ ብር መሰብሰብ መቻሉን አብራርተዋል።
የመድሀኒት ችግርን ለመፍታትም ከአርባምንጭ ጤና ሳይንስ ኮሌጅና ከጋሞ ልማት ማህበር ጋር በመሆን ተደራሽ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።
የመክፈል አቅምን መሰረት ያደረገ የክፍያ ስርዓትን ተግባራዊ በማድረግ ሁሉም ዜጋ ጤናውን እንዲያመርት እየተደረገ እንደሚገኝም ገልፀዋል።
የጋሞ ዞን አስተዳዳሪ አቶ አባይነህ አበራ እንዳሉት፤ በ2015/16 በተከታታይ ሁለት አመታት የተገኙ ድሎችን ለማስቀጠል በጋራ መስራት ይጠበቅብናል።
አገልግሎቱ አንዳችን ሌላችንን እንድንደግፍ የሚያደርግ ቢሆንም ከአሰራር ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮች እንዳሉ ጠቁመው ጉድለቶችን በማረም በዞኑ በጤናው ዘርፍ ለውጥ ማስመዝገብ እንደሚጠበቅ አመላክተዋል።
የአገልግሎት አሰጣጥና የመድሀኒት ችግር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ እንደሚገኝም ገልፀዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ተመኙህ ገረሱ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የልማትና መልካም አስተዳደር ተግባራትን ለማፋጠን ግብር ከፋዩ የሚጠበቅበትን ታክስ በወቅቱና በታማኝነት መክፈል እንዳለበት ተገለጸ
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ