የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት ቢሮ አመራሮች፣ ሰራተኞች እንዲሁም ለዞንና ለልዩ ወረዳ የስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ከፍል ቡድን መሪዎች በስነ-ምግባር እና በግዥ አስተዳደር ስርዓት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በወልቂጤ ከተማ እየተሰጠ ይገኛል።
የስልጠናውን መድረክ በንግግር የከፈቱት በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር መሃመድ ኑርዬ፤ መንገድና ትራንስፖርት ሁሉንም የሚመለከቱ በመሆናቸው ዘርፉ በመልካም ስነ-ምግባር እና ከሙስና በፀዳ መልኩ እንዲመራ የጋራ ጥረት የሚጠይቅ ተቋም መሆኑን ተናግረዋል።
በመድረኩ በተለያዩ አርእስቶች የተዘጋጁ ሰነዶች ቀርበው ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ እንዳልካቸው ደሳለኝ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
ሀገራዊ ምክክር፤ የመደማመጥ፣ የመግባባትና የጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት ነው!
ከ23 ሚሊየን በላይ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እንደሚተከሉ ተገለጸ
በግንቦት እና ሰኔ 2018 ዓ.ም ወራት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ፣ በቱሪዝም፣ በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በዲጂታል ኢትዮጵያ፣ በሀገር በቀል ሪፎርም እና ቀጣናዊ ዲፕሎማሲ ዙሪያ ላይ ያተኮሩ የተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ክንውኖችን አድርገዋል።