የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት ቢሮ አመራሮች፣ ሰራተኞች እንዲሁም ለዞንና ለልዩ ወረዳ የስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ከፍል ቡድን መሪዎች በስነ-ምግባር እና በግዥ አስተዳደር ስርዓት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በወልቂጤ ከተማ እየተሰጠ ይገኛል።
የስልጠናውን መድረክ በንግግር የከፈቱት በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር መሃመድ ኑርዬ፤ መንገድና ትራንስፖርት ሁሉንም የሚመለከቱ በመሆናቸው ዘርፉ በመልካም ስነ-ምግባር እና ከሙስና በፀዳ መልኩ እንዲመራ የጋራ ጥረት የሚጠይቅ ተቋም መሆኑን ተናግረዋል።
በመድረኩ በተለያዩ አርእስቶች የተዘጋጁ ሰነዶች ቀርበው ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ እንዳልካቸው ደሳለኝ – ከወልቂጤ ጣቢያችን
More Stories
ዲጂታል ኢትዮጵያን የመፍጠሪያ ጊዜን በማፋጠን ኢትዮጵያን የመጪው ዘመን መሪ ለማድረግ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
የሆሳዕና እናት ቃለ ህይወት ቤተክርስቲያን አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ ከአንድ መቶ በላይ ለሚሆኑ አቅመ ደካሞች የምግብ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገች
እመርታ ለዘላቂ ከፍታ!