ሀዋሳ፡ ታህሳስ 10/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የወልቂጤ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ ወደ ውጭ ለስራ ለሚሰማሩ ሰራተኞች እየሰጠ ባለው ስልጠና ብቃታቸውን የሚያጎለብት ዕውቀት ማግኘታቸውን ሰልጣኞቹ ገልጸዋል፡፡
የወልቂጤ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ በዚህ አመት ከ11ሺህ በላይ ሰራተኞችን ለማሰልጠን አቅዶ እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቋል።
በወልቂጤ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ የሰው ሀይል ልማት ፈፃሚ አቶ በሀይሉ አለሙ እንዳሉት፤ ከዚህ በፊት ወደ ውጭ ለስራ ለሚሰማሩ ከ1ሺህ 500 በላይ ሰራተኞችን መሰልጠናቸውን ጠቅሰው በተያዘው በጀት አመትም ከ11ሺህ በላይ ሰራተኞችን ለማሰልጠን ታቅዶ ወደ ተግባር ተገብቷል።
አቶ በሀይሉ አክለውም ከዚህ ቀደም የነበረው የምዝገባ ሂደት ኦንላይን ባለመሆኑ ይዘገይ እንደነበር አንስተው አሁን ላይ ችግሩ መቀረፉንም ጠቁመዋል።
በኮሌጁ የሆቴልና ቱሪዝም አሰልጣኝ መምህር አቶ አበበ አክለው በበኩላቸው፤ ለሰልጣኞች በተለያዩ ዘርፎች ስልጠናዎችን እየሰጡ መሆናቸውን ጠቅሰው ወደ ውጭ ለስራ የሚሄዱ ሰራተኞች ኮሌጁ ያመቻቸላቸውን እድል መጠቀም እንዳለባቸው አሳስበዋል።
በወልቂጤ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ ስልጠና ጨርሰው ሰርተፊኬት ለመውሰድ ከመጡ ሰልጣኞች መካከል የሺሀረግ ታዬ፣ ሰሚራ ሁሴን እና ሀምድያ በድሩ በሰጡት አስተያየት፤ ከልብስ ማጠብ ጀምሮ እስከ ምግብ ማብሰል የተግባር ስልጠና መውሰዳቸውን ጠቅሰው ይህም በራስ መተማመንን እንደሚጨምርላቸው ተናግረዋል።
ሰልጣኞቹ አክለውም ሰዎች በህገ ወጥ መንገድ ከመሰደድ ተቆጥበው መንግስት ባመቻቸላቸው እድል ተጠቃሚ መሆን እንደሚችሉ አስገንዝበዋል።
ዘጋቢ፡ አስፍር ሙህዲን – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ