በኢፌዴሪ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ የተመራ የአመራሮች ቡድን በአርባምንጭ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ተግባራትን ምልከታ አድርጓል
ሀዋሳ፡ ታህሳስ 04/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በኢፌዴሪ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ የተመራ የአመራሮች ቡድን በአርባምንጭ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ ፕሮጀክቶችንና የልማት ኢኒሼቲቮችን ምልከታ አድርጓል።
ቡድኑ በአርባምንጭ ከተማ እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት፣ በግንባታ ላይ የሚገኘውን የአርባምንጭ ከተማ ሁለገብ ስታዲየም ግንባታ እና በቅርቡ የተመረቀውን የጋሞ አደባባይ ተመልክተዋል።
በተጨማሪም በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የተሰማሩ እናት ሞሪንጋ ኢንተርፕራይዝ እና ያላ አግሮ ኢንዱስትሪ የወተት ማቀነባበሪያ ፋብሪካን ጎብኝተዋል።
በግንባታ ላይ የሚገኘው ስታዲየም የካፍ እና ፊፋ ስታንዳርዶችን ባሟላ መልኩ መገንባት እንዳለበትና አለምአቀፍ ወድድሮችን ወደ ከተማው ለማምጣት በሚያስችል አግባብ ሊሆን እንደሚገባ ሚኒስትሯ ጠቁመዋል።
ቡድኑ በጉብኝቱ ማጠቃለያ ለዞኑ እንዲሁም ለከተማዉ አመራሮች ግብረመልስ እንደሚሰጥ እንደሚጠበቅ የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ መረጃ ያመለክታል።

More Stories
ሀገራዊ ምክክር፤ የመደማመጥ፣ የመግባባትና የጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት ነው!
ከ23 ሚሊየን በላይ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እንደሚተከሉ ተገለጸ
በግንቦት እና ሰኔ 2018 ዓ.ም ወራት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ፣ በቱሪዝም፣ በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በዲጂታል ኢትዮጵያ፣ በሀገር በቀል ሪፎርም እና ቀጣናዊ ዲፕሎማሲ ዙሪያ ላይ ያተኮሩ የተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ክንውኖችን አድርገዋል።