በኢፌዴሪ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ የተመራ የአመራሮች ቡድን በአርባምንጭ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ተግባራትን ምልከታ አድርጓል
ሀዋሳ፡ ታህሳስ 04/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በኢፌዴሪ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ የተመራ የአመራሮች ቡድን በአርባምንጭ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ ፕሮጀክቶችንና የልማት ኢኒሼቲቮችን ምልከታ አድርጓል።
ቡድኑ በአርባምንጭ ከተማ እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት፣ በግንባታ ላይ የሚገኘውን የአርባምንጭ ከተማ ሁለገብ ስታዲየም ግንባታ እና በቅርቡ የተመረቀውን የጋሞ አደባባይ ተመልክተዋል።
በተጨማሪም በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የተሰማሩ እናት ሞሪንጋ ኢንተርፕራይዝ እና ያላ አግሮ ኢንዱስትሪ የወተት ማቀነባበሪያ ፋብሪካን ጎብኝተዋል።
በግንባታ ላይ የሚገኘው ስታዲየም የካፍ እና ፊፋ ስታንዳርዶችን ባሟላ መልኩ መገንባት እንዳለበትና አለምአቀፍ ወድድሮችን ወደ ከተማው ለማምጣት በሚያስችል አግባብ ሊሆን እንደሚገባ ሚኒስትሯ ጠቁመዋል።
ቡድኑ በጉብኝቱ ማጠቃለያ ለዞኑ እንዲሁም ለከተማዉ አመራሮች ግብረመልስ እንደሚሰጥ እንደሚጠበቅ የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ መረጃ ያመለክታል።

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ