ማንቸስተር ሲቲ በእንግሊዝ እግር ኳስ ታሪክ ከፍተኛ የተባለ ገቢ ማግኘቱ ተገለፀ
ሀዋሳ፡ ታህሳስ 04/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ማንቸስተር ሲቲ በእንግሊዝ እግር ኳስ ታሪክ ከፍተኛ የተባለ ዓመታዊ ገቢ ማግኘቱ ተገልጿል።
ባለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት የሊጉን ዋንጫ በማንሳት አዲስ ታሪክ ማፃፍ የቻለው ማንቸስተር ሲቲ በ2023/24 የውድድር ዓመት 715 ሚሊዮን ፓውንድ ገቢ ማግኘቱ ይፋ ተደርጓል።
የክለቡ ገቢ ከባለፈው ዓመት ገቢ በ2.2 ሚሊዮን ፓውንድ ጭማሪ ማሳየቱ ተነግሯል።
ክለቡ በዓመቱ ውስጥ የሁሊያን አልቫሬዝ፣ ጇኦ ካንሴሎን እና ሊያም ዴላፕን ዝውውር ሳይጨምር ከተጫዋቾቹ ሽያጭ 139 ሚሊዮን ፓውንድ ገቢ ማግኘቱ ተሰምቷል።
በተጨማሪም በጨዋታ ቀን 756 ሚሊዮን ፓውንድ ገቢ ማግኘቱ ሲገለፅ ከባለፈው ዓመት አንፃር የ3.7 ሚሊዮን ፓውንድ ጭማሪ አሳይቷል።
የእንግሊዙ ክለብ በአጠቃላይ በዓመቱ ውስጥ ከታክስ በፊት 73.8 ሚሊዮን ፓውንድ ትርፍ አግኝቻለሁ ብሏል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
ሀገር አቀፍ የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ያለምንም ችግር እንዲካሄድ በቂ ዝግጅት መደረጉን የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ ገለፁ
ዳራማሎ ደንዳሾ ስፖርት ክለብ ባስኬት ቡናን በማሸነፍ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለፍፃሜ ያለፉ ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል