በአመራሩና በፈጻሚ ደረጃ ያሉ ተግባራትን በተነሳሽነት መስራትና በጤናው ዘርፍ ያሉ ጉድለቶችን መለየት እንደሚገባ ተመላከተ
ሀዋሳ፡ ሕዳር 20/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በአመራሩና በፈጻሚ ደረጃ ያሉ ተግባራትን በተነሳሽነት መስራትና በጤናው ዘርፍ ያሉ ጉድለቶችን በመለየት ፈጣን አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ።
በቢሮው የእናቶችና ህጻናት ጤናና ስርአተ ምግብ ዳይሬክቶሬት የ2017 ዓ.ም የመጀመሪያ ሩብ አመት የአፈጻጻም ግምገማ መድረክ በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በመድረኩ ላይ የተገኙት የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ እንደገለፁት የህብረተሰቡ ጤና እንዲሻሻል በተለይም የእናቶችና ህጻናት ሞትን ለመቀነስ አገልግሎቱን ማዘመን ያስፈልጋል።
በጤናው ዘርፍ በተያዘው ሩብ አመት የተሻለ አፈጻጸም መመዝገቡንም ተጠቁሟል።
የሚሰጡ ክትባቶችን በጥራት ከመስጠት አኳያ ጠንካራ ክትትል በማድረግ የሚታይ ለውጥ ማምጣት ይገባልም ብለዋል።
ዘጋቢ፡ አስቻለው አማረ – ከወልቂጤ ጣቢያችን
More Stories
በካፋ ዞን ጨና ወረዳ በምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም (FSRP) የተከናወኑ የልማት ስራዎች ላይ ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ጋር የልምድ ልውውጥ ተደረገ
ሳታ ቴክኖሎጂ እና ቢዝነስ ኮሌጅ በአርባ ምንጭ ካምፓስ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች በመጀመሪያ ዲግሪ እና ቴክኒክና ሙያ ስልጠና መስኮች ያሰለጠናቸውን 2 ሺህ 132 ተማሪዎችን አስመረቀ
በዕቅድ የሚመራ የመፈፀም አቅሙ ያደገ ሲቪል ሰርቫንት ለመገንባት እየተሰራ መሆኑን በደቡብ ኦሞ ዞን የሳላማጎ ወረዳ ሲቪል ሰርቪስ ጽ/ቤት ገለፀ