በአመራሩና በፈጻሚ ደረጃ ያሉ ተግባራትን በተነሳሽነት መስራትና በጤናው ዘርፍ ያሉ ጉድለቶችን መለየት እንደሚገባ ተመላከተ
ሀዋሳ፡ ሕዳር 20/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በአመራሩና በፈጻሚ ደረጃ ያሉ ተግባራትን በተነሳሽነት መስራትና በጤናው ዘርፍ ያሉ ጉድለቶችን በመለየት ፈጣን አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ።
በቢሮው የእናቶችና ህጻናት ጤናና ስርአተ ምግብ ዳይሬክቶሬት የ2017 ዓ.ም የመጀመሪያ ሩብ አመት የአፈጻጻም ግምገማ መድረክ በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በመድረኩ ላይ የተገኙት የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ እንደገለፁት የህብረተሰቡ ጤና እንዲሻሻል በተለይም የእናቶችና ህጻናት ሞትን ለመቀነስ አገልግሎቱን ማዘመን ያስፈልጋል።
በጤናው ዘርፍ በተያዘው ሩብ አመት የተሻለ አፈጻጸም መመዝገቡንም ተጠቁሟል።
የሚሰጡ ክትባቶችን በጥራት ከመስጠት አኳያ ጠንካራ ክትትል በማድረግ የሚታይ ለውጥ ማምጣት ይገባልም ብለዋል።
ዘጋቢ፡ አስቻለው አማረ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
ህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምርጫ ማኒፌስቶ፣ የዕጩ ማስተዋወቂያ እንዲሁም የምርጫ ቅስቀሳ ፕሮግራም በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ አካሄደ
ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጥራት ያለው የአይን ህክምና በሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገለፀ
ብልጽግና ፓርቲ የማህበረሰቡ ችግር የሚቀርፉ ፕሮጀክቶችን ገንብቶ በማጠናቀቅ በውጤታማነት ለአገልግሎት እያበቃ ነው – ዶ/ር መሀመድ ኑርዬ