በአመራሩና በፈጻሚ ደረጃ ያሉ ተግባራትን በተነሳሽነት መስራትና በጤናው ዘርፍ ያሉ ጉድለቶችን መለየት እንደሚገባ ተመላከተ
ሀዋሳ፡ ሕዳር 20/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በአመራሩና በፈጻሚ ደረጃ ያሉ ተግባራትን በተነሳሽነት መስራትና በጤናው ዘርፍ ያሉ ጉድለቶችን በመለየት ፈጣን አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ።
በቢሮው የእናቶችና ህጻናት ጤናና ስርአተ ምግብ ዳይሬክቶሬት የ2017 ዓ.ም የመጀመሪያ ሩብ አመት የአፈጻጻም ግምገማ መድረክ በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በመድረኩ ላይ የተገኙት የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ እንደገለፁት የህብረተሰቡ ጤና እንዲሻሻል በተለይም የእናቶችና ህጻናት ሞትን ለመቀነስ አገልግሎቱን ማዘመን ያስፈልጋል።
በጤናው ዘርፍ በተያዘው ሩብ አመት የተሻለ አፈጻጸም መመዝገቡንም ተጠቁሟል።
የሚሰጡ ክትባቶችን በጥራት ከመስጠት አኳያ ጠንካራ ክትትል በማድረግ የሚታይ ለውጥ ማምጣት ይገባልም ብለዋል።
ዘጋቢ፡ አስቻለው አማረ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የህፃናት የወደፊት የኑሮ ሁኔታ እንዲሻሻልና የተሻለ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ለመገንባት እየሠራ እንደሚገኝ የጉራጌ ህዝብ ራስ አገዝ ልማት ድርጅት ገለፀ
5ኛው አገራዊ የሠላም ኮንፈረንስን በተመለከተ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት የኮሙኒኬሽን አገልግሎት የተላለፈ መልዕክት
ፈጣን ፣ ወቅታዊ እና ተአማኒ መረጃን ተደራሽ ለማድረግ ዘመኑን የሚመጥን አሰራርን መዘርጋት እንደሚገባ ተገለጸ