በአመራሩና በፈጻሚ ደረጃ ያሉ ተግባራትን በተነሳሽነት መስራትና በጤናው ዘርፍ ያሉ ጉድለቶችን መለየት እንደሚገባ ተመላከተ
ሀዋሳ፡ ሕዳር 20/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በአመራሩና በፈጻሚ ደረጃ ያሉ ተግባራትን በተነሳሽነት መስራትና በጤናው ዘርፍ ያሉ ጉድለቶችን በመለየት ፈጣን አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ።
በቢሮው የእናቶችና ህጻናት ጤናና ስርአተ ምግብ ዳይሬክቶሬት የ2017 ዓ.ም የመጀመሪያ ሩብ አመት የአፈጻጻም ግምገማ መድረክ በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በመድረኩ ላይ የተገኙት የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ እንደገለፁት የህብረተሰቡ ጤና እንዲሻሻል በተለይም የእናቶችና ህጻናት ሞትን ለመቀነስ አገልግሎቱን ማዘመን ያስፈልጋል።
በጤናው ዘርፍ በተያዘው ሩብ አመት የተሻለ አፈጻጸም መመዝገቡንም ተጠቁሟል።
የሚሰጡ ክትባቶችን በጥራት ከመስጠት አኳያ ጠንካራ ክትትል በማድረግ የሚታይ ለውጥ ማምጣት ይገባልም ብለዋል።
ዘጋቢ፡ አስቻለው አማረ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ