ሀዋሳ፡ ሕዳር 18/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በዓሉን በንግግር የከፈቱት የማረቆ ልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጀማል አማሮ በንግግራቸው በዓሉን ስናከብር አንድ የሚያደርጉንን ሁነቶች በማጠናከር ሊሆን ይገባል ብለዋል
የተዛብ ትርክቶች የህዳሴ ጉዟችንን እንዳያሰናክልብን ጥንቃቄ ልናደርግ ይገባል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው የማይታዩ ድንበር ዘለል እጆች በሚጥሯቸው ውጅንብሮች ሳንደናገር አንድነታችንን በማረጋገጥ ሰላማችነንን ማፅናት ይገባናል ብለዋል
የብሄር ብሄረሰቦች ቀን ህገ- መንግስታችን ያጎናፀፈን የእኩልነታችንና የአንድነታችን ማህተም መሆኑን የገለፁት የልዩ ወረዳው ዋና አፈ ጉባዔ ሻምበል ደበሮ ይህንን የብዙሀን የትግል ውጤት ለማፅናት ሁላችንም የሰላም አምባሳደር ልንሆን ይገባናል ብለዋል።
የብሄር ብሄረሰቦች ቀን እርስ በእርስ እንድንተዋወቅ ባህል ወግ ስርዓቶቻችንን እንድናስተዋውቅ እድል የፈጠረ መሆኑን የገለፁት የልዩ ወረዳው ባህልና ቱሪዝም ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሊሬ አሌዬ በበኩላቸውም ህብብራዊነት ላስጌጣት ሀገር የብሄር ብሄረሰብ በዓል አላማ በየዕለት ተእለት እንቀሳቀሴያችን ሊተገበር የሚገባው ጉዳይ ነው ብለዋል ።
በዓሉ ከምስራቅ ጉራጌ ዞን እና አጉራባች ዞንና ወረዳዋች ከመጡ እንግዶች ጋር በተለያዩ የኪነጥበ ስራዎች በደመቀ ሁኔታ ተከብሯል
ዘጋቢ : ሰብስቤ አደም

More Stories
ህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምርጫ ማኒፌስቶ፣ የዕጩ ማስተዋወቂያ እንዲሁም የምርጫ ቅስቀሳ ፕሮግራም በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ አካሄደ
ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጥራት ያለው የአይን ህክምና በሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገለፀ
ብልጽግና ፓርቲ የማህበረሰቡ ችግር የሚቀርፉ ፕሮጀክቶችን ገንብቶ በማጠናቀቅ በውጤታማነት ለአገልግሎት እያበቃ ነው – ዶ/ር መሀመድ ኑርዬ