የብልጽግና ፓርቲ አምስተኛ ዓመት የምስረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ በመንግስትና ልማታዊ ባለሀብቶች የጋራ ትብብር ውጤታማ የሆኑ ተቋማት ተጎበኙ
በልማታዊ ባለሀብቶች የተሠሩ የቆፌ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የማስፋፊያ ግንባታዎችና የዳራሮ ሁለተኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤት አሁናዊ የመማር ማስተማር ሥራ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልልና በጌዴኦ ዞን ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ጥሪ በተደረገላቸው በበዓሉ ታዳሚዎች ተጎብኝተዋል፡፡
የትምህርቱን ዘርፍ ስብራት ለመጠገን መንግስት የጀመራቸውን ጥረቶች ከማስቀጠል አኳያ ልማታዊ ባለሀብቶች የማይተካ ሚና እያበረከቱ በመሆናቸው ያላቸውን ልባዊ አክብሮት የጌዴኦ ዞን አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡
የግንባታ ሂደቱ እየተፋጠነ የሚገኘው የዞኑ አስተዳደር ህንፃ ጉብኝቱ ከተካሄደባቸው ተቋማት አንዱ ሲሆን ህንፃው ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ምቹ የሥራ አካባቢን ከመፍጠር ባለፈ የዞኑን ገፅታ ከመቀየር አኳያም ከፍተኛ ፋይዳ ያለው መሆኑ ተመላክቷል፡፡
ዘጋቢ: ሳሙኤል በቀለ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምርጫ ማኒፌስቶ፣ የዕጩ ማስተዋወቂያ እንዲሁም የምርጫ ቅስቀሳ ፕሮግራም በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ አካሄደ
ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጥራት ያለው የአይን ህክምና በሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገለፀ
ብልጽግና ፓርቲ የማህበረሰቡ ችግር የሚቀርፉ ፕሮጀክቶችን ገንብቶ በማጠናቀቅ በውጤታማነት ለአገልግሎት እያበቃ ነው – ዶ/ር መሀመድ ኑርዬ