የብልጽግና ፓርቲ አምስተኛ ዓመት የምስረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ በመንግስትና ልማታዊ ባለሀብቶች የጋራ ትብብር ውጤታማ የሆኑ ተቋማት ተጎበኙ
በልማታዊ ባለሀብቶች የተሠሩ የቆፌ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የማስፋፊያ ግንባታዎችና የዳራሮ ሁለተኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤት አሁናዊ የመማር ማስተማር ሥራ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልልና በጌዴኦ ዞን ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ጥሪ በተደረገላቸው በበዓሉ ታዳሚዎች ተጎብኝተዋል፡፡
የትምህርቱን ዘርፍ ስብራት ለመጠገን መንግስት የጀመራቸውን ጥረቶች ከማስቀጠል አኳያ ልማታዊ ባለሀብቶች የማይተካ ሚና እያበረከቱ በመሆናቸው ያላቸውን ልባዊ አክብሮት የጌዴኦ ዞን አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡
የግንባታ ሂደቱ እየተፋጠነ የሚገኘው የዞኑ አስተዳደር ህንፃ ጉብኝቱ ከተካሄደባቸው ተቋማት አንዱ ሲሆን ህንፃው ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ምቹ የሥራ አካባቢን ከመፍጠር ባለፈ የዞኑን ገፅታ ከመቀየር አኳያም ከፍተኛ ፋይዳ ያለው መሆኑ ተመላክቷል፡፡
ዘጋቢ: ሳሙኤል በቀለ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ