በነዳጅ ምርቶች ስርጭት ላይ የሚታየውን ሕገ ወጥ አሠራር ለማረም በትኩረት እየሠራ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድ እና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ
በግብይት ወቅት የሚስተዋሉ ሕገ ወጥ አሠራሮችን ለማስተካከል ሕብረተሰቡ የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።
መንግሥት የጀመራቸውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን ምክንያት በማድረግ በምርቶች ላይ ያልተገባ ጭማሪ በማድረግ የኑሮ ውድነቱ እንዲባባስ የሚያደርጉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድ እና ገበያ ልማት ቢሮ ሐላፊ አቶ ገለቦ ጎልቶሞ አሳስበዋል።
በተለይም በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች የነዳጅ ምርቶችን በሕገወጥ መንገድ ከማደያዎች በማውጣት የሕብረተሰቡ ቅሬታ እንዲጨምር በሚያደርጉ አካላት ላይ በተደራጀ ሁኔታ የእርምት እርምጃ እየተወሰደ ነውም ብለዋል የቢሮ ሀላፊው።
የወላይታ ዞን ንግድ እና ገበያ ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ ሀይለ ስላሴ፤ በዞኑ ባለፉት ሶስት ወራት ብቻ ከ65 ሺህ ሊትር በላይ ቤንዚን በሕገወጥ መንገድ ሲዘዋወር መያዙን ገልጸው ሰሞኑን ደግሞ በዞኑ ኦፋ ወረዳ ገሱባ ከተማ ከኩንቢ ማደያ 11 ሺህ ሊትር ቤንዚን በሦስት መኪናዎች ተጭኖ ሲወጣ በቁጥጥር ስር መዋሉን ገልጸዋል።
የነዳጅ ምርቶች ፍላጎት መጨመር ጋር በተያያዘ የመጣውን ምርት በአግባቡ ሣያደርሱ ለሕገ ወጥነት መነሻ በሚሆኑ ነጋዴዎች ላይ መንግሥት የማያዳግም ርምጃ መውሰዱን እንዲቀጥል ያነጋገርናቸው ተጠቃሚዎች ጠይቀዋል።
በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች ያሉ ማደያዎች የሚመጣውን ነዳጅ በፍትሐዊነት ተደራሽ እንዲያደርጉ በግብረ ሐይል የቁጥጥር ሥራው እየተካሔደ መሆኑም ታውቋል።
ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሁሉንም የመማሪያ መጻሕፍት ባለማግኘታቸው በትምህርታቸው ላይ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቆንጋና ቆቄ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ