19ኛው የብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በይርጋጨፌ ከተማ አስተዳደር በተለያዩ ኩነቶች ተከበረ
ሀዋሳ፡ ሕዳር 16/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) 19ኛው የብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ከተማ አስተዳደር በተለያዩ ኩነቶች ተከብሯል፡፡
የብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን መከበር ዜጎች በልዩነት መካከል አንድነታቸውን እንዲያጠናክሩ እንደሚያግዝ የበዓሉ ታዳሚዎች ገልፀዋል፡፡
የይርጋጨፌ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳዊት የጋ በዓሉን አስመልክቶ ሠነድ ባቀረቡበት ወቅት እንደተናገሩት፤ የፌደራሊዝም አለመዳበር ብዝሃ ማንነቶችን ማስተናገድ ላይ ክፍተቶችን አምጥቷል፡፡
ይሁን እንጂ ዜጎች ልዩነቶችን እንደ እድል ተጠቅመው የነገዋን ኢትዮጵያ በጋራ መገንባት እንደሚችሉም አብራርተዋል፡፡
የይርጋጨፌ ከተማ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ታዬ ታደሰ በበኩላቸው፤ የብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን መከበር የሁሉም ብሔር ባህል፣ ቋንቋና ታሪክ እንዲጎለብት ትልቅ አስተዋውፅኦ እንዳለው ተናግረዋል።
እንደ አፈ ጉባኤው ገለጻ፤ የይርጋጨፌ ከተማ ከሃያ ስድስት በላይ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩባት መሆኗን በማብራራት ሁሉም የጋራ ማንነቶችን በማዳበር ልዩነቶችን እንደ ፀጋ በመቀበል ለከተማው እድገትና ሠላም የድርሻውን እየተወጣ ነው ብለዋል፡፡
ዘጋቢ፡ አብነት አበበ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሁሉንም የመማሪያ መጻሕፍት ባለማግኘታቸው በትምህርታቸው ላይ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቆንጋና ቆቄ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ