ዩኒቨርሲቲው በአካባቢው ከሚገኙና አለማቀፍ ከሆኑ 69 ያክል ተቋማትና ኢንዱስትሪ ማዕከላት ጋር ትስስር ፈጥሮ እየሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከኢንደስትሪ ተቋማት ጋር በህጋዊ ማዕቀፍ በታገዘ የጋራ ዕቅድ ማስተሳሰር የትምህርት አሰጣጡ በተግባር እንዲደገፍ ከማድረግ አልፎ በምርምር ስራዎችም እንዲጎለብት የሚያስችል መሆኑን በመጥቀስ፤ ይህንኑ እውን ለማድረግ የተዘጋጀ የውይይት መድረክ መሆኑን ነው በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የጂንካ ዩኒቨርሲቲ የምርምር ዓለማቀፋዊነትና አጋርነት ዳይሬክተር ዶ/ር ኮማንደር መሐመድ ገልጸዋል።
ከተቋማት ጋር የተፈጠሩ ትስስሮች በተናጥል የሚደረገውን ሩጫ ቅንጅታዊ እንዲሆን በማድረግ ያለውን የሰው ሃይል በአግባቡ ለመጠቀም የሚኖረው ፋይዳ የጎላ መሆኑንም አስምረውበታል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አምባ ጩፋ በበኩላቸው ከምርምር ተቋማትና ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በጋራ መስራት ተቋማትን ለጋራ ግብ የጋራ አቅም በመፍጠር የጋራ ውጤታማነትን እንዲረጋገጥ የሚያስል መሆኑን ተናግረዋል።
ስለዚህም ዩኒቨርሲቲው ከተቋማቱ ጋር የመሰረተው ትስስር ከመግባቢያ ሰነድ ፊርማ የተሻገረ ውጤታማ እንዲሆን ለማስቻል በትኩረት እየተከናወነ የሚገኝ ተግባር ስለመሆኑም አንስተዋል።
ይህ መድረክም ለተጀመሩ የፕሮጀክት ትግበራ ስራዎች ውጤታማነት የኢንዱስትሪ ተቋማትን ማዕከል የማድረጉ ጅምር ስራ በመፈተሽ ወደ ውጤት ለማሻገር ያለመ መሆኑን ጠቅሰው ባለድርሻ አካላትም የድርሻቸው ሊወጡ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በመድረኩ ቴክኒክና ሙያ ከአጎራባች ዞኖች ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮችን ጨምሮ በአቅራቢያ የሚገኙ የምርምር ተቋማትና የኢንደስትሪ ማዕከላት እንዲሁም መንግስታዊ ያልሆኑ አጋር ድርጅቶችና የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተሳታፊዎች ሆነዋል።
ዘጋቢ ፡ ዳኜ ጥላሁን- ከጂንካ ቅርንጫፍ ጣቢያ
More Stories
አካል ጉዳተኞች መብቶቻቸውና ጥቅሞቻቸውን ለማስጠበቅ በቅንጅትና በጥምረት መስራት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለፀ
አካባቢን በመጠበቅና በማጽዳት ምቹና ጽዱ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ሁሉም የድርሻውን ልወጣ እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አሳሰቡ
ግለሰባዊ ነጠላ ትርክቶችን በጋራ በመታገል በመደመር እሳቤ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ ተገለጸ