የ19ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓልን በአርባ ምንጭ ከተማ የሚገኙ የሚዲያ ተቋማት አከበሩ።
ኢትዮጵያ በህዝቦች ብዝሀነት የተመሠረተች በቋንቋ፣ በባህልና በሀይማኖት ረገድ ያላት ልዩነት ውበቷ ሆኖ እነሆ ዘመናትን ተሻግራለች።
የጋሞ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ሠላማዊት ቦዳ እንደተናገሩት፤ ልዩነታችን አንድነታችን ነው ስንል የአንዳችን መኖር ለአንዳችኝ ዋስትና እንዲሁም ሀገራችን የተያያዘችውን የብለፅግና ጉዞ ከዳር ለማድረስ ህብረ ብሔራዊ አንድነታችን ሚናው የላቀ ነው።
ባለፉት 19 አመታት በሀገሪቱ የሚገኙ ብሔር ብሔረሰቦች አንድነታቸው ተጠብቆ ያላቸውን ባህልና እሴት በማስተዋወቁ ረገድ ሚዲያዎች ከፍተኛ ሚና ከመጫወታቸው በዘለለ በራሳቸው ቋንቋ ሚዲያውን መጠቀም እንዲችሉ መደረጉ ተሰፋ ሰጪ ተግባር ሆኖ ዘልቋል ብለዋል።
በሌላ በኩል ያሉንን ልዩነቶችን ተጠቅመው የህዝቦችን ነባርና ጠንካራ መስተጋብርን ለግጭትና ለሠላም እጦት የሚጠቀሙ አካላትን የማስገንዘብ፣ የማስጠንቀቅና የህዝቦች አንድነት በጠንካራ አለት ላይ የተገነባ መሠረት እንዲሆን ማሳወቅ ከሚዲያ አካላት ይጠበቃል ብለዋል ወ/ሮ ሠላማዊት።
ወ/ሮ ሠላማዊት አያይዘውም የሚዲያ ተቋማትና ባለሙያዎች ብሔር ብሔረሰቦች ያላቸውን እምቅ የባህል፣ የአኗኗርና ሌሎች እሴቶቻቸውን ቱባውን ሳይለቅ ለአለም ማስተዋወቅ የተሰጣቸው ሀገራዊ አደራ ስለመሆኑም አስገንዝበዋል።
19ኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በአርባ ምንጭ ከተማ ሲከበር እንግዶች በሚኖራቸው ቆይታ የማይረሳ ትውስታ ይዘው ይመለሱ ዘንድ የሚዲያ ባለሙያዎች ሚና ተኪ የሌለው ነውም ብለዋል።
በመጨረሻም በአሉን የተመለከተ ሠነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
ዘጋቢ፡ በኃይሉ ሙሉጌታ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን
More Stories
አካል ጉዳተኞች መብቶቻቸውና ጥቅሞቻቸውን ለማስጠበቅ በቅንጅትና በጥምረት መስራት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለፀ
አካባቢን በመጠበቅና በማጽዳት ምቹና ጽዱ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ሁሉም የድርሻውን ልወጣ እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አሳሰቡ
ግለሰባዊ ነጠላ ትርክቶችን በጋራ በመታገል በመደመር እሳቤ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ ተገለጸ