በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀዲያ ዞን ሌሞ ወረዳ በ85 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባ የነዳጅ ማዳያ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
በዞኑ 429 ባለሃብቶች በግብርና፣በኢንዱስትሪና በአገልግሎት ዘርፍ መሰመራታቸውም መረጀዎች አመልካቷል ፡፡
በሀዲያ ዞን የሌሞ ወረዳ ዋና አስተደደሪ አቶ ታደለ ደምሴ እንደተናገሩት መንግስት የኢንቨስትመንት እና የንግዱን ማህበረሰብ ለማበረታታትና ለመደገፍ ባለሃብቶች በመረጡት የስራ ዘርፎች እንዲሰማሩ ምቹ ሁኔታ እየፈጠረ ይገኛል ብለዋል::
የነዳጅ ማደያው ባለቤት አቶ ጌታቸው ገዕናሞ የነዳጅ ማደያው ግንባታ ከ85 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደፈጀ ገልጸዋል::
ለ15 ቋሚና ለ50 ጊዜያዊ ዜጎች የስራ ዕድል ፈጥሯል ፡፡በቀጣይም ከማደያው ጎን ለጎን በኢንዱስትሪ ዘርፍ የፋብሪካ ግንባታ ስራ ለመጀመር ዕቅድ እንዳላቸውም ገልጸዋል ።
የሀዲያ ዞን የኢንቨስትመንትና የኢንዱስትሪ ልማት መምሪያ ኃላፍ አቶ ታምራት ሜግሶ በበኩላቸው በዞኑ 429 ባለሃብቶች በግብርና፣በኢንዱስትሪና በአገልግሎት ዘርፍ መሰመራታቸውን ጠቅሰው፣ፕሮጀክቶቹም በስራ ዕድል ፈጠራና በቴክኖሎጂ ሽግግር ለዜጎች ከፍተኛ አስተዋጽኦ እየበረከቱ ይገኛል ብለዋል::
የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቴዎስ አኒዮ በበኩላቸው የመጣውን ነዳጅ በአግባቡ በመጠቀም ለታለመለት አላማ ማዋል እንዳለበት ተናግረዉ፣ ባለድርሻ አካላትም ህገ ወጥ ተግባራት እንዳይከናወን ቁጥጥር ማድረግ አለባቸው ብለዋል።
ወደ ዞኑ ለሚመጡ ሌሎች ባለሀብቶችም መሬት ከመስጠት ጀምሮ መንግስት አስፈለጊውን ድጋፍ በማድረግ እንደሚያበረታታ አቶ ማቴዎስ አረጋግጠዋል።
ዘጋቢ፡በየነ ሰላሙ-ከሆሳዕና ጣቢያችን
More Stories
ቆሻሻን በአግባቡ በማስወገድ ከተማዋ ፅዱና ውብ እንድትሆን የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ነው – የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በቋሚነት የሚደገፉበት ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የቡርጂ ዞን አስተዳደር አስታወቀ
“አንድ ሰው ወደዚህች ምድር ሲመጣ እንዲሰራ የተፈቀደለትና የሚጠበቅበት ነገር አለ” – ታደሰ ገብሬ /ጃክሰን/