የፀረ ተህዋሲያን መድሃኒቶች መላመድ ለሰው ልጆች ስጋት እየሆነ መምጣቱን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታውቋል።
ቢሮው የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሃላፊዎችና ባለሙያዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ የፀረ-ተህዋሲያን መድሃኒቶች በጀርሞች መላመድን መከላከል ላይ ያተኮረ የንቅናቄ መድረክ በቡታጅራ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
በዓለም አቀፍ ደረጃ የጸረ ተህዋስያን መድኃኒቶች ያለ አግባብ ስራ ላይ በመዋላቸው መድኃኒቶቹ ከተህዋስያን ጋር በቀላሉ እንዲላመዱ እንደሚያስችላቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
በመድረኩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ሀብቴ ገ/ሚካኤል፤ የፀረ-ተህዋሲያን መድሃኒቶች መላመድ ለሰው ልጆች ስጋት እየሆነ መምጣቱን አስታውቀዋል።
በዚህም በየዓመቱ በጸረ ተህዋስያን መድኃኒት መላመድ ምክንያት በዓለማችን ከ1 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ለህልፈት እንደሚዳረጉ ሀላፊው አመላክተዋል፡፡
በፀረ ተህዋሲያን መድሃኒቶች መላመድ ምክንያት ብዙ ዋጋ ተከፍሎባቸውና ዓመታትን ወስደው የተገኙ መድሃኒቶችን ዋጋ ቢስ የሚያደርግ ሲሆን ይህም በሽታውን ለማከም አስቸጋሪ እንደሚያደርግ አስረድተዋል፡፡
እንደ ሀገር በዘርፉ እየተስተዋለ ያለውን ችግር ለመቅረፍ ሰፊ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቁመው ለስኬታማነቱ ደግሞ የሁሉም ባለድርሻ አካላት እጅና ጓንት ሆኖ መሥራት ወሳኝ መሆኑን ነው አቶ ሀብቴ ያስገነዘቡት።
ከህዳር 9 እስከ 15 የጸረ ተህዋስያን መድኃኒት በጀርሞች መላመድን ለመቀነስ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሳምንት “እናስተምር፣ እናሳውቅ፣ አሁን እንተግብር” በሚል ሀሳብ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከበረ ይገኛል፡፡
ዘጋቢ፡ መሐመድ ሽሁር – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ