የፀረ ተህዋሲያን መድሃኒቶች መላመድ ለሰው ልጆች ስጋት እየሆነ መምጣቱን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታውቋል።
ቢሮው የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሃላፊዎችና ባለሙያዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ የፀረ-ተህዋሲያን መድሃኒቶች በጀርሞች መላመድን መከላከል ላይ ያተኮረ የንቅናቄ መድረክ በቡታጅራ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
በዓለም አቀፍ ደረጃ የጸረ ተህዋስያን መድኃኒቶች ያለ አግባብ ስራ ላይ በመዋላቸው መድኃኒቶቹ ከተህዋስያን ጋር በቀላሉ እንዲላመዱ እንደሚያስችላቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
በመድረኩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ሀብቴ ገ/ሚካኤል፤ የፀረ-ተህዋሲያን መድሃኒቶች መላመድ ለሰው ልጆች ስጋት እየሆነ መምጣቱን አስታውቀዋል።
በዚህም በየዓመቱ በጸረ ተህዋስያን መድኃኒት መላመድ ምክንያት በዓለማችን ከ1 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ለህልፈት እንደሚዳረጉ ሀላፊው አመላክተዋል፡፡
በፀረ ተህዋሲያን መድሃኒቶች መላመድ ምክንያት ብዙ ዋጋ ተከፍሎባቸውና ዓመታትን ወስደው የተገኙ መድሃኒቶችን ዋጋ ቢስ የሚያደርግ ሲሆን ይህም በሽታውን ለማከም አስቸጋሪ እንደሚያደርግ አስረድተዋል፡፡
እንደ ሀገር በዘርፉ እየተስተዋለ ያለውን ችግር ለመቅረፍ ሰፊ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቁመው ለስኬታማነቱ ደግሞ የሁሉም ባለድርሻ አካላት እጅና ጓንት ሆኖ መሥራት ወሳኝ መሆኑን ነው አቶ ሀብቴ ያስገነዘቡት።
ከህዳር 9 እስከ 15 የጸረ ተህዋስያን መድኃኒት በጀርሞች መላመድን ለመቀነስ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሳምንት “እናስተምር፣ እናሳውቅ፣ አሁን እንተግብር” በሚል ሀሳብ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከበረ ይገኛል፡፡
ዘጋቢ፡ መሐመድ ሽሁር – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ