ሀዋሳ፡ ሕዳር 14/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ 120 የህክምና ዶክተሮችን አስመርቋል፡፡
ከተመራቂዎቹ መካከል 67ቱ ወንዶች ሲሆኑ 53 ደግሞ ሴቶች ናቸው።
በምረቃ ስነስርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ዶክተር ችሮታው አየለ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ህዝባችን በቂ የህክምና ይፈልጋል፤ ባልተመቻቸ ሁኔታ ያስተማረንን ህብረተሰብ በቀናነት እና በታማኝነት ማገልገል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ኮሌጁ ከመማር ማስተማር ተግባሩ ጎን ለጎን በሪፈራል ሆስፒታሉ በርካታ ሺህ ለሚቆጠሩ የሲዳማ እና አጎራባች ህዝቦች አግልግሎት እየሰጠ ስለመሆኑ አንስተው አገልግሎቱን ለማጠናከርና ለማስፋፋት እየተሰራን ነው ብለዋል።
የኮሌጁ ኤክስኪዩቲቭ ዳይረክተር ተባባሪ ፕሮፌሰር አለሙ ጠሚሶ በበኩላቸው፤ ኮሌጁ ለሀገሪቱ ጤና ዘርፉ መጎልበት ያላሳለሰ ጥረት እያደረገ ነው ብለዋል።
ኮሌጁ ባለፉት አመታት ብቻ 2ሺህ 3 መቶ የህክምና ዶክተሮችን በማስተማርና በማሰልጠን ወደ ስራው አለም መቀላቀሉን ጠቅሰዋል።
የዕለቱ የክብር እንግዳና የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ሀላፊ ዶክተር ሰላማዊ መንገሻ፤ የኢትዮጵያ ህዝብን የጤና ዘርፍ ጥያቄዎችን የመመለስ አዲስ ተመራቂዎች ሀላፊነት አለባችሁ ነው ያሉት።
ተመራቂዎች ወደ ህብረተሰቡ ሲቀላቀሉ በአገልጋይነት እና በአመስጋኝነት መንፈስ እንዲያገለግሉም አሳስበዋል።
ዘጋቢ፡ ጀማል የሱፍ
More Stories
ቆሻሻን በአግባቡ በማስወገድ ከተማዋ ፅዱና ውብ እንድትሆን የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ነው – የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በቋሚነት የሚደገፉበት ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የቡርጂ ዞን አስተዳደር አስታወቀ
“አንድ ሰው ወደዚህች ምድር ሲመጣ እንዲሰራ የተፈቀደለትና የሚጠበቅበት ነገር አለ” – ታደሰ ገብሬ /ጃክሰን/