ሀዋሳ፡ ሕዳር 14/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ 120 የህክምና ዶክተሮችን አስመርቋል፡፡
ከተመራቂዎቹ መካከል 67ቱ ወንዶች ሲሆኑ 53 ደግሞ ሴቶች ናቸው።
በምረቃ ስነስርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ዶክተር ችሮታው አየለ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ህዝባችን በቂ የህክምና ይፈልጋል፤ ባልተመቻቸ ሁኔታ ያስተማረንን ህብረተሰብ በቀናነት እና በታማኝነት ማገልገል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ኮሌጁ ከመማር ማስተማር ተግባሩ ጎን ለጎን በሪፈራል ሆስፒታሉ በርካታ ሺህ ለሚቆጠሩ የሲዳማ እና አጎራባች ህዝቦች አግልግሎት እየሰጠ ስለመሆኑ አንስተው አገልግሎቱን ለማጠናከርና ለማስፋፋት እየተሰራን ነው ብለዋል።
የኮሌጁ ኤክስኪዩቲቭ ዳይረክተር ተባባሪ ፕሮፌሰር አለሙ ጠሚሶ በበኩላቸው፤ ኮሌጁ ለሀገሪቱ ጤና ዘርፉ መጎልበት ያላሳለሰ ጥረት እያደረገ ነው ብለዋል።
ኮሌጁ ባለፉት አመታት ብቻ 2ሺህ 3 መቶ የህክምና ዶክተሮችን በማስተማርና በማሰልጠን ወደ ስራው አለም መቀላቀሉን ጠቅሰዋል።
የዕለቱ የክብር እንግዳና የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ሀላፊ ዶክተር ሰላማዊ መንገሻ፤ የኢትዮጵያ ህዝብን የጤና ዘርፍ ጥያቄዎችን የመመለስ አዲስ ተመራቂዎች ሀላፊነት አለባችሁ ነው ያሉት።
ተመራቂዎች ወደ ህብረተሰቡ ሲቀላቀሉ በአገልጋይነት እና በአመስጋኝነት መንፈስ እንዲያገለግሉም አሳስበዋል።
ዘጋቢ፡ ጀማል የሱፍ

More Stories
በግንቦት እና ሰኔ 2018 ዓ.ም ወራት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ፣ በቱሪዝም፣ በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በዲጂታል ኢትዮጵያ፣ በሀገር በቀል ሪፎርም እና ቀጣናዊ ዲፕሎማሲ ዙሪያ ላይ ያተኮሩ የተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ክንውኖችን አድርገዋል።
በህገወጥ መንገድ ከሀገር መውጣት ከህግ፣ ከደህንነት እና ከማህበራዊ አንፃር ከባድ ችግሮችን እንደሚያስከትል ተገለጸ
ወጣቶች ያላቸውን ጊዜ፣ እውቀትና ጉልበት በመጠቀም አቅመ ደካሞችንና የተቸገሩ ወገኖችን መደገፍ እንዳለባቸው ተገለፀ