ሀዋሳ፡ ሕዳር 13/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጌዴኦ ዞን በሚገኙ ሁሉም ትምህርት ቤቶች የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በተለያዩ ኩነቶች መከበሩን የጌዴኦ ዞን ትምህርት መምሪያ ገልጿል።
የጌዴኦ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ዘማች ክፍሌ የዕለቱን መከበር አስመልክቶ ለደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ይርጋጨፌ ቅርንጫፍ በሰጡት አስተያየት በዞኑ ሁሉም ትምህርት ቤቶች በዓሉ አንድነትን በሚያጠናክሩና የብሔረሶቦችን የጋራ እሴት በሚገልፁ ኩነቶች መከበሩን አስታውቀዋል፡፡
የዲላ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዮሴፍ ሆርዶፋ በበኩላቸው፤ በዓሉ ትውልዱ አንድነትን ከሚሸረሽሩ አስተሳሰቦች በመራቅ በጋራ ማደግ በሚቻልበት መንገድ ስብዕናውን እንዲገነባ ትልቅ ፋይዳ ያለው መሆኑን አስረድተዋል፡፡
በዓሉ በዞኑ ባሉ ሁሉም ትምህርት ቤቶች በትምህርታዊና አዝናኝ ኩነቶች መከበሩ ተመላክቷል፡፡
ዘጋቢ: ሳሙኤል በቀለ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
ቆሻሻን በአግባቡ በማስወገድ ከተማዋ ፅዱና ውብ እንድትሆን የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ነው – የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በቋሚነት የሚደገፉበት ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የቡርጂ ዞን አስተዳደር አስታወቀ
“አንድ ሰው ወደዚህች ምድር ሲመጣ እንዲሰራ የተፈቀደለትና የሚጠበቅበት ነገር አለ” – ታደሰ ገብሬ /ጃክሰን/