ሀዋሳ፡ ሕዳር 13/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጌዴኦ ዞን በሚገኙ ሁሉም ትምህርት ቤቶች የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በተለያዩ ኩነቶች መከበሩን የጌዴኦ ዞን ትምህርት መምሪያ ገልጿል።
የጌዴኦ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ዘማች ክፍሌ የዕለቱን መከበር አስመልክቶ ለደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ይርጋጨፌ ቅርንጫፍ በሰጡት አስተያየት በዞኑ ሁሉም ትምህርት ቤቶች በዓሉ አንድነትን በሚያጠናክሩና የብሔረሶቦችን የጋራ እሴት በሚገልፁ ኩነቶች መከበሩን አስታውቀዋል፡፡
የዲላ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዮሴፍ ሆርዶፋ በበኩላቸው፤ በዓሉ ትውልዱ አንድነትን ከሚሸረሽሩ አስተሳሰቦች በመራቅ በጋራ ማደግ በሚቻልበት መንገድ ስብዕናውን እንዲገነባ ትልቅ ፋይዳ ያለው መሆኑን አስረድተዋል፡፡
በዓሉ በዞኑ ባሉ ሁሉም ትምህርት ቤቶች በትምህርታዊና አዝናኝ ኩነቶች መከበሩ ተመላክቷል፡፡
ዘጋቢ: ሳሙኤል በቀለ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ