ሀዋሳ፡ ሕዳር 13/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጌዴኦ ዞን በሚገኙ ሁሉም ትምህርት ቤቶች የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በተለያዩ ኩነቶች መከበሩን የጌዴኦ ዞን ትምህርት መምሪያ ገልጿል።
የጌዴኦ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ዘማች ክፍሌ የዕለቱን መከበር አስመልክቶ ለደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ይርጋጨፌ ቅርንጫፍ በሰጡት አስተያየት በዞኑ ሁሉም ትምህርት ቤቶች በዓሉ አንድነትን በሚያጠናክሩና የብሔረሶቦችን የጋራ እሴት በሚገልፁ ኩነቶች መከበሩን አስታውቀዋል፡፡
የዲላ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዮሴፍ ሆርዶፋ በበኩላቸው፤ በዓሉ ትውልዱ አንድነትን ከሚሸረሽሩ አስተሳሰቦች በመራቅ በጋራ ማደግ በሚቻልበት መንገድ ስብዕናውን እንዲገነባ ትልቅ ፋይዳ ያለው መሆኑን አስረድተዋል፡፡
በዓሉ በዞኑ ባሉ ሁሉም ትምህርት ቤቶች በትምህርታዊና አዝናኝ ኩነቶች መከበሩ ተመላክቷል፡፡
ዘጋቢ: ሳሙኤል በቀለ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምርጫ ማኒፌስቶ፣ የዕጩ ማስተዋወቂያ እንዲሁም የምርጫ ቅስቀሳ ፕሮግራም በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ አካሄደ
ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጥራት ያለው የአይን ህክምና በሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገለፀ
ብልጽግና ፓርቲ የማህበረሰቡ ችግር የሚቀርፉ ፕሮጀክቶችን ገንብቶ በማጠናቀቅ በውጤታማነት ለአገልግሎት እያበቃ ነው – ዶ/ር መሀመድ ኑርዬ