ሀዋሳ፡ ሕዳር 13/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጌዴኦ ዞን በሚገኙ ሁሉም ትምህርት ቤቶች የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በተለያዩ ኩነቶች መከበሩን የጌዴኦ ዞን ትምህርት መምሪያ ገልጿል።
የጌዴኦ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ዘማች ክፍሌ የዕለቱን መከበር አስመልክቶ ለደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ይርጋጨፌ ቅርንጫፍ በሰጡት አስተያየት በዞኑ ሁሉም ትምህርት ቤቶች በዓሉ አንድነትን በሚያጠናክሩና የብሔረሶቦችን የጋራ እሴት በሚገልፁ ኩነቶች መከበሩን አስታውቀዋል፡፡
የዲላ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዮሴፍ ሆርዶፋ በበኩላቸው፤ በዓሉ ትውልዱ አንድነትን ከሚሸረሽሩ አስተሳሰቦች በመራቅ በጋራ ማደግ በሚቻልበት መንገድ ስብዕናውን እንዲገነባ ትልቅ ፋይዳ ያለው መሆኑን አስረድተዋል፡፡
በዓሉ በዞኑ ባሉ ሁሉም ትምህርት ቤቶች በትምህርታዊና አዝናኝ ኩነቶች መከበሩ ተመላክቷል፡፡
ዘጋቢ: ሳሙኤል በቀለ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በግንቦት እና ሰኔ 2018 ዓ.ም ወራት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ፣ በቱሪዝም፣ በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በዲጂታል ኢትዮጵያ፣ በሀገር በቀል ሪፎርም እና ቀጣናዊ ዲፕሎማሲ ዙሪያ ላይ ያተኮሩ የተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ክንውኖችን አድርገዋል።
በህገወጥ መንገድ ከሀገር መውጣት ከህግ፣ ከደህንነት እና ከማህበራዊ አንፃር ከባድ ችግሮችን እንደሚያስከትል ተገለጸ
ወጣቶች ያላቸውን ጊዜ፣ እውቀትና ጉልበት በመጠቀም አቅመ ደካሞችንና የተቸገሩ ወገኖችን መደገፍ እንዳለባቸው ተገለፀ